ሞትን ፡ የረታ ፡ ጌታ (Moten Yereta Gieta) - ካሌብ ፡ ተስፋዬ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ካሌብ ፡ ተስፋዬ
(Caleb Tesfaye)

Lyrics.jpg


(5)

ሞትን ፡ የረታ ፡ ጌታ
(Moten Yereta Gieta)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

(5)

ርዝመት (Len.): 5:46
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የካሌብ ፡ ተስፋዬ ፡ አልበሞች
(Albums by Caleb Tesfaye)

አዝ፦ ሞትን ፡ የረታ ፡ ጌታ ፡ ነው ፡ የምናመልከው
የዲያቢሎስን ፡ ክፉ ፡ ሥራ ፡ ያፈረሰው
አልተሸነፈም ፡ አይሸነፍም ፡ አይተነዋል
አምላካችንን ፡ ንጉሣችንን ፡ ማን ፡ ይመስለዋል (፪x)

የዓለም ፡ መድኃኒት ፡ ይሄን ፡ ትሁት
ቢደፋ ፡ አንገቱን ፡ ቀላል ፡ አርገውት
እውር ፡ ሲያበራ ፡ ዲዳ ፡ ሲያናግር
በክፉ ፡ አናት ፡ ላይ ፡ እሳት ፡ ሲጭር
ተደንቀው ፡ አዩት ፡ ኧረ ፡ ይሄስ ፡ ማነው
አውሎ ፡ ንፋሱን ፡ ወጀቡን ፡ የሚያዘው

አዝ፦ ሞትን ፡ የረታ ፡ ጌታ ፡ ነው ፡ የምናመልከው
የዲያቢሎስን ፡ ክፉ ፡ ሥራ ፡ ያፈረሰው
አልተሸነፈም ፡ አይሸነፍም ፡ አይተነዋል
አምላካችንን ፡ ንጉሣችንን ፡ ማን ፡ ይመስለዋል

ትክክለኛ ፡ ሰራተኛ
ሽንገላ ፡ የሌለበት ፡ እውነተኛ
ሃሰተኞች ፡ ቢያደናብሩ
ቃሉን ፡ በተንኮል ፡ ቢመነዝሩ
ልቡ ፡ አይደነግጥ ፡ ምንም ፡ ቢሆን ፡ አይፈራ
በአደባባይ ፡ በግልጥ ፡ አለ ፡ እየሰራ

አዝ፦ ሞትን ፡ የረታ ፡ ጌታ ፡ ነው ፡ የምናመልከው
የዲያቢሎስን ፡ ክፉ ፡ ሥራ ፡ ያፈረሰው
አልተሸነፈም ፡ አይሸነፍም ፡ አይተነዋል
አምላካችንን ፡ ንጉሣችንን ፡ ማን ፡ ይመስለዋል

ያንበረከከ ፡ መተተኞችን
በሰው ፡ ላይ ፡ የሚጫወቱ ፡ ጠንቋዮችን
ጓዛቸውን ፡ ጥለው ፡ ፈረጠጡ
በቁጣው ፡ ጅራፍ ፡ እየተቀጡ
ጌታ ፡ ነን ፡ ያሉ ፡ የታል ፡ አቅማቸው
ወድቀው ፡ ቀሩ ፡ እንጂ ፡ ሲነሱ ፡ አላየናቸው

አዝ፦ ሞትን ፡ የረታ ፡ ጌታ ፡ ነው ፡ የምናመልከው
የዲያቢሎስን ፡ ክፉ ፡ ሥራ ፡ ያፈረሰው
አልተሸነፈም ፡ አይሸነፍም ፡ አይተነዋል
አምላካችንን ፡ ንጉሣችንን ፡ ማን ፡ ይመስለዋል

ወረት ፡ መስሏቸው ፡ የነገራቸው
በሶስተኛው ፡ ቀን ፡ እነሳለሁ ፡ ሲላቸው
መሳቂያ ፡ አደረጉት ፡ መሳለቂያ
ምን ፡ ልታመጣ ፡ ከእንግዲህ ፡ ወዲያ
የጠበቃት ፡ ቀን ፡ ደረሰችና
አናወጣቸው ፡ ከሞት ፡ ተነሳና

አዝ፦ ሞትን ፡ የረታ ፡ ጌታ ፡ ነው ፡ የምናመልከው
የዲያቢሎስን ፡ ክፉ ፡ ሥራ ፡ ያፈረሰው
አልተሸነፈም ፡ አይሸነፍም ፡ አይተነዋል
አምላካችንን ፡ ንጉሣችንን ፡ ማን ፡ ይመስለዋል (፪x)