በእሳት ፡ ውስጥ (Besat West) - ካሌብ ፡ ተስፋዬ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ካሌብ ፡ ተስፋዬ
(Caleb Tesfaye)

Lyrics.jpg


(5)

ሞትን ፡ የረታ ፡ ጌታ
(Moten Yereta Gieta)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

(7)

ርዝመት (Len.): 5:24
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የካሌብ ፡ ተስፋዬ ፡ አልበሞች
(Albums by Caleb Tesfaye)

አዝ፦ በእሳት ፡ ውስጥ ፡ አልፌ ፡ አላቃጠለኝም
በውኃ ፡ ውስጥ ፡ አልፌ ፡ አላሰጠመኝም
የትናንቱ ፡ ኢየሱስ ፡ ዛሬም ፡ አልተወኝም
እጁ ፡ እጄን ፡ ይዞታል ፡ አለቀቀኝም
እጁ ፡ እጄን ፡ ይዞታል ፡ አለቀቀኝም (፪x)

ወጀቡን ፡ ተው ፡ አውሎ ፡ ነፋሱንም
እየገሰጸ ፡ ረዳኝ ፡ አልተወኝም
አሻገረኝ ፡ ወዲያ ፡ ወዲያ ፡ ማዶ
አልመሸብኝ ፡ መጥቶልኛል ፡ ማልዶ

አዝ፦ በእሳት ፡ ውስጥ ፡ አልፌ ፡ አላቃጠለኝም
በውኃ ፡ ውስጥ ፡ አልፌ ፡ አላሰጠመኝም
የትናንቱ ፡ ኢየሱስ ፡ ዛሬም ፡ አልተወኝም
እጁ ፡ እጄን ፡ ይዞታል ፡ አለቀቀኝም (፪x)

አብሮኝ ፡ ሲጓዝ ፡ ሜዳ ፡ ተራራውን
መቼም ፡ ቢሆን ፡ አልረሳም ፡ ውለታዉን
እያስቻለኝ ፡ ልቤን ፡ እያሰፋ
ደጋገፈኝ ፡ ያዘኝ ፡ እንዳልጠፋ

አዝ፦ በእሳት ፡ ውስጥ ፡ አልፌ ፡ አላቃጠለኝም
በውኃ ፡ ውስጥ ፡ አልፌ ፡ አላሰጠመኝም
የትናንቱ ፡ ኢየሱስ ፡ ዛሬም ፡ አልተወኝም
እጁ ፡ እጄን ፡ ይዞታል ፡ አለቀቀኝም (፪x)

አቤት ፡ ስንቱን ፡ ስንቱን ፡ አሳለፈኝ
እየከለለ ፡ ክፉ ፡ እንዳያገኘኝ
ጐኔ ፡ ባይቆም ፡ ለሁለ ፡ ባቄ ፡ ነኝ
ማዕበሉ ፡ ወጀቡ ፡ በከደነኝ

አዝ፦ በእሳት ፡ ውስጥ ፡ አልፌ ፡ አላቃጠለኝም
በውኃ ፡ ውስጥ ፡ አልፌ ፡ አላሰጠመኝም
የትናንቱ ፡ ኢየሱስ ፡ ዛሬም ፡ አልተወኝም
እጁ ፡ እጄን ፡ ይዞታል ፡ አለቀቀኝም (፪x)

አይዞህ ፡ ባዬ ፡ አጽናኜ ፡ ጌታዬ
የሰላም ፡ ምንጭ ፡ ደስታዬ ፡ እርካታዬ
ተወጣሁት ፡ ጉልበቴ ፡ ኃይል ፡ ሆኖ
አላፈረም ፡ ማንም ፡ እርሱን ፡ ተማምኖ

አዝ፦ በእሳት ፡ ውስጥ ፡ አልፌ ፡ አላቃጠለኝም
በውኃ ፡ ውስጥ ፡ አልፌ ፡ አላሰጠመኝም
የትናንቱ ፡ ኢየሱስ ፡ ዛሬም ፡ አልተወኝም
እጁ ፡ እጄን ፡ ይዞታል ፡ አለቀቀኝም (፪x)