የተወጋ ፡ ጐኑን (Yetewega Gonun) - ብዙ ፡ ሙሉጌታ ፡ እና ፡ ወንጌላዊ ፡ ተድላ ፡ አሰፋ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ብዙ ፡ ሙሉጌታ ፡ እና ፡ ወንጌላዊ ፡ ተድላ ፡ አሰፋ
(Bezu Mulugeta)

Lyrics.jpg


(2)

ኢየሱስ ፡ ልዩ ፡ ነው ፡ አልን! እንደገና
(Eyesus Leyu New Alen Endegena)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፩ (1998)
ቁጥር (Track):

(5)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የብዙ ፡ ሙሉጌታ ፡ እና ፡ ወንጌላዊ ፡ ተድላ ፡ አሰፋ ፡ አልበሞች
(Albums by Bezu Mulugeta)

አዝ፦ የተወጋ ፡ ጐኑን ፡ እጆቼ ፡ ሲነካ
እይኖቼ ፡ በሩልኝ ፡ ሕይወት ፡ አለው ፡ ለካ
እንደሞተ ፡ አልቀረም ፡ ኢየሱስ ፡ ተነስቷል
ለሞተው ፡ ነገሬ ፡ ሕያው ፡ ነፍስን ፡ ዘርቷል

፩) መቃብር ፡ አትሂዱ ፡ የሱስ ፡ በዚያ ፡ የለም
ሕያው ፡ ሆኗል ፡ እሱ ፡ ሕያው ፡ ለዘላለም
እጆቹን ፡ ነክቸ ፡ እኔ ፡ ፈውስ ፡ አገኘሁ
ስለዚህ ፡ ተነስቷል ፡ ተነስቷል ፡ እላለሁ

አዝ፦ የተወጋ ፡ ጐኑን ፡ እጆቼ ፡ ሲነካ
እይኖቼ ፡ በሩልኝ ፡ ሕይወት ፡ አለው ፡ ለካ
እንደሞተ ፡ አልቀረም ፡ ኢየሱስ ፡ ተነስቷል
ለሞተው ፡ ነገሬ ፡ ሕያው ፡ ነፍስን ፡ ዘርቷል

፪) ዐይኖቸ ፡ አይተውታል ፡ ኢየሱስ ፡ ተነስቷል
በልብ ፡ ጓዳዬ ፡ በኑሮዬ ፡ ገብቷል
አትፍራ ፡ ብሎ ፡ አለኝ ፡ ዳሰኝ ፡ ቅረብና
አዎ ፡ ሕያው ፡ ሆኗል ፡ ኢየሱስ ፡ እንደገና

አዝ፦ የተወጋ ፡ ጐኑን ፡ እጆቼ ፡ ሲነካ
እይኖቼ ፡ በሩልኝ ፡ ሕይወት ፡ አለው ፡ ለካ
እንደሞተ ፡ አልቀረም ፡ ኢየሱስ ፡ ተነስቷል
ለሞተው ፡ ነገሬ ፡ ሕያው ፡ ነፍስን ፡ ዘርቷል

፫) ዛሬስ ፡ አምሮበታል ፡ ባባቱ ፡ ቀኝ ፡ አለ
ሁሉን ፡ በመታዘዝ ፡ ስለተቀበለ
ከሥም ፡ ሁሉ ፡ በላይ ፡ ስምም ፡ ተሰጥቶታል
ፍጥረት ፡ ሁሉ ፡ የሱስ ፡ ጌታ ፡ ነህ ፡ ይሉታል

አዝ፦ የተወጋ ፡ ጐኑን ፡ እጆቼ ፡ ሲነካ
እይኖቼ ፡ በሩልኝ ፡ ሕይወት ፡ አለው ፡ ለካ
እንደሞተ ፡ አልቀረም ፡ ኢየሱስ ፡ ተነስቷል
ለሞተው ፡ ነገሬ ፡ ሕያው ፡ ነፍስን ፡ ዘርቷል

፬) ተስፋ ፡ እንደሌለው ፡ እንበታተንም
ሰብሳቢ ፡ ቃል ፡ አለው ፡ እኛ ፡ አንወድቅም
የሞተ ፡ የማይሰማ ፡ አምላክ ፡ አናመልክም
ይሰራል ፡ ተነስቷል ፡ ሕያው ፡ ነው ፡ ዘላለም

አዝ፦ የተወጋ ፡ ጐኑን ፡ እጆቼ ፡ ሲነካ
እይኖቼ ፡ በሩልኝ ፡ ሕይወት ፡ አለው ፡ ለካ
እንደሞተ ፡ አልቀረም ፡ ኢየሱስ ፡ ተነስቷል
ለሞተው ፡ ነገሬ ፡ ሕያው ፡ ነፍስን ፡ ዘርቷል