አሻግረኸናል (Ashagerehenal) - ብዙ ፡ ሙሉጌታ ፡ እና ፡ ወንጌላዊ ፡ ተድላ ፡ አሰፋ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ብዙ ፡ ሙሉጌታ ፡ እና ፡ ወንጌላዊ ፡ ተድላ ፡ አሰፋ
(Bezu Mulugeta)

Lyrics.jpg


(2)

ኢየሱስ ፡ ልዩ ፡ ነው ፡ አልን! እንደገና
(Eyesus Leyu New Alen Endegena)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፩ (1998)
ቁጥር (Track):

(10)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የብዙ ፡ ሙሉጌታ ፡ እና ፡ ወንጌላዊ ፡ ተድላ ፡ አሰፋ ፡ አልበሞች
(Albums by Bezu Mulugeta)

አሻግረኸናል ፡ ባሕሩን
ከፍለህልናል ፡ ውሃውን
ፈታችን ፡ ሆነህ ፡ ስትመራን
ማንም ፡ አልቻለም ፡ ሊያቆመን

አረ ፡ ፡ እንዳንተ ፡ ያለ ፡ በሰማይ
ማን ፡ ነው ፡ ይፈለግ ፡ የበላይ
ምድርና ፡ ሞላው ፡ ያንተ ፡ ነው
ለሕዝብ ፡ ሞገስ ፡ የሆንከው

ችግራችን ፡ የአንተ ፡ ችግር
ሃዘናችን ፡ የአንተ ፡ ሀዘን
ነበር ፡ ለካ ፡ የኛ ፡ ጌታ
ምትክ ፡ ሆንከን ፡ በኛ ፡ ፈንታ
እስከ ፡ መስቀል ፡ ወደድከን
ከሞት ፡ ወደ ፡ ሕይወት ፡ ተሻገርን

ተሸከምነው ፡ የኛን ፡ በደል
፡፡ለዘላለም ፡ ኢየሱስ ፡ ክበር (፪x)

ስንደክም ፡ ስትበረታ
ስንወድቅ ፡ ሲታገለን
ማን ፡ ነው ፡ እንዳንተ ፡ የቻለን
አለሁ ፡ ያለ ፡ ያልታዬን

ወረት ፡ ከቶ ፡ የማያውቅ
ኢየሱስ ፡ ብቻ ፡ ተባረክ (፬x)

ሆድ ፡ ሲብሰን ፡ ይገባሃል
ብሶታችን ፡ ይሰማሃል
ከስትንፋስ ፡ ይልቅ ፡ ቅርብ ፡ ነህ
ለእኛ ፡ አንተ ፡ ታስባለህ
ከናት ፡ በላይ ፡ አሳዳጊ
ትዕግሥተኛና ፡ አሳላፊ

የተጐዳን ፡ አስታማሚ
ሰው ፡ አድርጐ ፡ ለክብር ፡ ሿሚ

ባሕሩ ፡ ሲቆም ፡ ፊታችን
ፈርኦን ፡ ሲሮጥ ፡ ኋላችን
አንተ ፡ ነህ ፡ ለእኛ ፡ የደረስክ
ውሃውን ፡ ለሁለት ፡ የከፈልክ
ልባችን ፡ በአንተ ፡ አረፈ
አሳዳጃችን ፡ አፈረ

መርጦናል ፡ ባንተ ፡ መደገፍ
በምንም ፡ ነገር ፡ ብናልፍ