አምልኮዬ (Amlekoyie) - ብዙ ፡ ሙሉጌታ ፡ እና ፡ ወንጌላዊ ፡ ተድላ ፡ አሰፋ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ብዙ ፡ ሙሉጌታ ፡ እና ፡ ወንጌላዊ ፡ ተድላ ፡ አሰፋ
(Bezu Mulugeta)

Lyrics.jpg


(2)

ኢየሱስ ፡ ልዩ ፡ ነው ፡ አልን! እንደገና
(Eyesus Leyu New Alen Endegena)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፩ (1998)
ቁጥር (Track):

(2)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የብዙ ፡ ሙሉጌታ ፡ እና ፡ ወንጌላዊ ፡ ተድላ ፡ አሰፋ ፡ አልበሞች
(Albums by Bezu Mulugeta)

በወሬ ፡ አይደለም ፡ እኛ ፡ የሰማነው
በሕይወታችን ፡ እልፍ ፡ ጌታ ፡ አደረገው
ልዩ ፡ አፍቃሪ ፡ ወዳጅ ፡ አባት ፡ እግኝተናል
ልናመልክ ፡ ልንሰግድ ፡ በፊቱ ፡ ወጥተናል

ላምልከው ፡ እያልኩኝ ፡ እወደዋለሁኝ
የመስቀሉን ፡ ሚስጥር ፡ ፍቅር ፡ እያየሁኝ
ውለታው ፡ ስለእኔ ፡ እጅግ ፡ በዝቶልናል
እኔ ፡ አበዛለሁ ፡ ለሥሙ ፡ ምስጋና

እርሱ ፡ ብቻ ፡ አምላክ ፡ አባት ፡ ሆኖአልና
ይገባል ፡ ለስሙ ፡ አምልኮ ፡ ምሥጋና
ስጡት ፡ ከልባችሁ ፡ አብዙለት ፡ ዘምሩ
ብቻውን ፡ ይመለክ ፡ ይወራለት ፡ ክብሩ

የተነሱበትን ፡ ጥሎ ፡ አዋረዳቸው
ሥልጣኑን ፡ ቀምቶ ፡ ባዶ ፡ አደረጋቸው
እነማን ፡ በርትተው ፡ እግዚአብሔርን ፡ ሻሩ
እርሱ ፡ እኮ ፡ ይኖራል ፡ በነበረ ፡ ክብሩ

 ፡ ፡ ፡ ሥልጣኑ ፡ እጅግ ፡ ትልቅ ፡ ነው
 ፡ ፡ ፡ ፈቅጄ ፡ እመልከዋለሁ
 ፡ ፡ ፡ ወድጄ ፡ እምበረከካለሁ
 ፡ ፡ ፡ ልናገር ፡ ከምችለው ፡ በላይ
 ፡ ፡ ፡ ትልቅ ፡ ነው ፡ የክንዱ ፡ ሥልጣን
 ፡ ፡ ፡ ገብቶኛል ፡ እዘምራለሁ
 ፡ ፡ ፡ ሥልጣኑ ፡ ከማንም ፡ በላይ ፡ ነው
 ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ስልጣኑ

ኃያል ፡ ነን ፡ ጐበዝ ፡ ነን ፡ እያሉ
በእርሱ ፡ ላይ ፡ ብዙ ፡ ፎረኩ
ታገሰ ፡ ዘመን ፡ ሰጣቸው
ታበዩ ፡ ክንዱ ፡ አጠፋቸው
በዘመኑ ፡ በታሪክ ፡ የለም
ስላጣኑ ፡ ፍፁም ፡ አልተሻረም

እንዴት ፡ ልናወጥ ፡ እንዴትስ ፡ ልፍራ
እያየሁ ፡ የክንዱን ፡ ስራ
ተደላድዬ ፡ ቆሜያለሁ
ኃያሉን ፡ ክንዱን ፡ ይዣለሁ
ሊሰራ ፡ እርሱ ፡ ሲነሳ
እያየሁ ፡ ሁሉም ፡ ይታዘዛል
 ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ስልጣኑ