Bethlehem Wolde/Cher Neh/Cher Neh

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

በቀራንዮ መስቀል ላይ ስራዬን አንተ ሰርተሃል ቀንበሬን አንተ ሰበርከው እዳዬን ከኔ አስወገድከው (፪)

ቸር ነህ ለኔ ቸር ነህ (፪x) ቸር ነህ ጌታዬ ቸር ነህ ቸር ነህ ለኔ ቸር ነህ

ለኔ እንዳንተ ማን አለኝ የውስጤ ልቤን የሚረዳልኝ ስለኔ ሁሌ ታስባለህ በአብ ዘንድ ትማልዳለህ

ብዙ ብዙ ነው ቸርነትህ ብዙ ነው ብዙ ብዙ ነው በጐነትህ ብዙ ነው ብዙ ብዙ ነው ምህረትህ ብዙ ነው ብዙ ብዙ ነው ይቅርታህ ብዙ ነው

በደሙ አጥቦ አንጽቶ ሕይወቴንም ለውጦ ሰው አደረገኝ ረድኤቴ እኔም ላክብረው ከልቤ (፪x)

ቸር ነህ ለኔ ቸር ነህ ቸር ነህ ለኔ ቸር ነህ ቸር ነህ ጌታዬ ቸር ነህ ቸር ነህ ለኔ ቸር ነህ

ብዙ ብዙ ነው ቸርነትህ ብዙ ነው ብዙ ብዙ ነው በጐነትህ ብዙ ነው ብዙ ብዙ ነው ምህረትህ ብዙ ነው ብዙ ብዙ ነው ይቅርታህም ብዙ ነው(፪)