ተፈፀመ (Tefetseme) - ቤተልሔም ፡ ተዘራ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ቤተልሔም ፡ ተዘራ
(Bethlehem Tezera)

Bethlehem Tezera 2.jpeg


(2)

ተፈፀመ
(Tefetseme)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፯ (2005)
ቁጥር (Track):

(4)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የቤተልሔም ፡ ተዘራ ፡ አልበሞች
(Albums by Bethlehem Tezera)

ጥንቅቅ ፡ አድርጐ ፡ ስራዬን ፡ ሰራልኝ፡ (ተፈፀመ)
እዳዬን ፡ በደሙ ፡ አወራረደልኝ ፡ (ተፈፀመ)
እውነትና ፡ ምሕረቱም ፡ ተስማሙልኝ ፡ (ተፈፀመ)
ዘላለመ ፡ በርሱ ፡ ቀን ፡ ተወሰነልኝ ፡ (ተፈፀመ)

የማረፊያ ፡ አረገው ፡ ዘላለሜን ፡ የማረፍያ ፡ አረገው (፫x)
የደም ፡ ላብ ፡ እያላበው ፡ ፍቅር ፡ ግድ ፡ ስላለው (፪x)

እንወደው ፡ ዘንድ ፡ እንኳ ፡ ደምግባት ፡ እስኪያጣ ፡ (ተፈፀመ)
የህማም ፡ ሰው ፡ ሆነ ፡ በደዌ ፡ ተመታ ፡ (ተፈፀመ)
እንዲህ ፡ ባለመውደድ ፡ እንዲህ ፡ ባለፍቅር ፡ (ተፈፀመ)
እራሱን ፡ አሳየኝ ፡ አምኜው ፡ እንድኖር ፡ (ተፈፀመ)

የማረፊያ ፡ አረገው ፡ ዘላለሜን ፡ የማረፍያ ፡ አረገው (፫x)
የደም ፡ ላብ ፡ እያላበው ፡ ፍቅር ፡ ግድ ፡ ስላለው (፪x)

አብ ፡ አስቀድሞ ፡ በልጁ ፡ ወሰነኝ ፡ (ተፈፀመ)
ወስኖም ፡ መረጠኝ ፡ ሊያፀድቀኝ ፡ (ተፈፀመ)
የቃሉን ፡ ብርሃን ፡ በልቤ ፡ አበራው ፡ (ተፈፀመ)
አድራሻዬን ፡ ሊያደርግ ፡ በሰማዩ ፡ ስፍራ ፡ (ተፈፀመ)

የደስታ ፡ አረገው ፡ ዘላለሜን ፡ የደስታ ፡ አረገው (፪x)
የእፎይታ ፡ አረገው ፡ ዘላለሜን ፡ የእፎይታ ፡ አረገው (፪x)
የደም ፡ ላብ ፡ እያላበው ፡ ፍቅር ፡ ግድ ፡ ስላለው (፪x)

ተፈፀመ ፡ ተፈፀመ ፡ ተፈፀመ ፡ ተፈፀመ (፪x)