እግዚአብሔር ፡ አለ (Egziabhier Ale) - ቤተልሔም ፡ ተዘራ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ቤተልሔም ፡ ተዘራ
(Bethlehem Tezera)

Bethlehem Tezera 2.jpeg


(2)

ተፈፀመ
(Tefetseme)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፯ (2005)
ቁጥር (Track):

(6)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የቤተልሔም ፡ ተዘራ ፡ አልበሞች
(Albums by Bethlehem Tezera)

የጭንቁ ፡ ጊዜ ፡ ሳይመጣ ፡ ግዳጅ ፡ ሳይሆንብኝ
አመልካለሁ ፡ በውዴታ ፡ አየተገዛሁ ፡ ለጌታ (፪x)

ግዴታዬን ፡ ለማክበር ፡ አይደለም ፡ የማመሰግነው
ይልቁንም ፡ ፍቅሩ ፡ ጨምሮብኝ ፡ አጣሁኝ ፡ የምለው (፪x)

ሳይወዱ ፡ ጌታ ፡ ነህ ፡ ቢሉት ፡ ቀን ፡ አስገድዷቸው
እኔ ፡ አስቲ ፡ ልዘምርለት ፡ ምቹ ፡ ሳለ ፡ ጊዜው (፪x)

ስንት ፡ የምለው ፡ ነገር ፡ በልቤ ፡ የለኝ
ቃላት ፡ አቅም ፡ አጣ ፡ ተቸገርኩ ፡ እያነሰብኝ
እኔ ፡ ከማቀርበው ፡ እልፍ ፡ የምስጋና ፡ ቃል
የእግዚአብሔር ፡ የአንድ ፡ ቀን ፡ ምሕረቱ ፡ ይመዝንብኛል

የሚያሳስበኝ ፡ እሱን ፡ አንዴት ፡ እንደማከብር ፡ ነው
የሚያሳስበኝ ፡ እሱን ፡ አንዴት ፡ እንደማስከብር ፡ ነው
የሚያሳስበኝ ፡ ጌታን ፡ አንዴት ፡ እንደማከብር ፡ ነው
የሚያሳስበኝ ፡ እሱን ፡ አንዴት ፡ እንደማስከብር ፡ ነው

ነገር ፡ ጐደለ ፡ እግዚአብሔር ፡ አለ
ኑሮም ፡ ጐደለ ፡ እግዚአብሔር ፡ አለ (፪x)

አንዳንድ ፡ ጊዜ ፡ አይደለም ፡ የማመሰግነው
ሲጐልም ፡ እሰየሁ ፡ ሲሞላም ፡ እሰየሁ
የማመሰግንበት ፡ ምክንያቴ ፡ የእግዚአብሔር ፡ ነው (፪x)

ጌታ ፡ ካለ ፡ ቤቴ ፡ ሙሉ ፡ ነው (፪x)
እጠግባለሁ ፡ ፊቱን ፡ እያየሁ (፪x)
እሱ ፡ ካለ ፡ ቤቴ ፡ ሙሉ ፡ ነው (፪x)
እጠግባለሁ ፡ ፊቱን ፡ እያየሁ (፪x)

የሚያሳስበኝ ፡ አንተን ፡ አንዴት ፡ እንደማከብር ፡ ነው
የሚያሳስበኝ ፡ አንተን ፡ አንዴት ፡ እንደማስከብር ፡ ነው (፪x)

አፌን ፡ ሞልቼ ፡ እንድዘምረው
የሚጋብዘኝ ፡ ማንነትህ ፡ ነው (፪X)

ለማንነትህ ፡ ክብር ፡ ይድረስህ
ለማንነትህ ፡ ክብር ፡ ይሁንልህ
ለማንነትህ ፡ ክብር ፡ ይኸውልህ
ለማንነትህ ፡ ክብር ፡ ይሁንልህ

ነገር ፡ ጐደለ ፡ እግዚአብሔር ፡ አለ
ኑሮም ፡ ጐደለ ፡ እግዚአብሔር ፡ አለ (፫x)