እያባበለኝ (Eyababelegn) - ቤተልሔም ፡ ተዘራ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ቤተልሔም ፡ ተዘራ
(Bethlehem Tezera)

Bethlehem Tezera 3.jpg


(3)

ዕድሜዬ ፡ በቤትህ ፡ ይለቅ
(Edmieyie Bebieteh Yileq)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፱ (2007)
ቁጥር (Track):

፲ ፫ (13)

ርዝመት (Len.): 7:24
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የቤተልሔም ፡ ተዘራ ፡ አልበሞች
(Albums by Bethlehem Tezera)

ቀን ፡ ጠብቆ ፡ ገሸሽ፡ ይልብኝ ፡ ይሆን ፡ ወይ?
አለልኝ ፡ ስል ፡ ዓይንሽ/ህ ፡ ለአፈር ፡ ይለኛል ፡ ወይ?
ብዬ ፡ እንዳልል ፡ እንዳልሰጋበት ፡ ዛሬም
አብሮኝ ፡ አለ ፡ ቤቴ ፡ ባይመቸውም
ብዬ ፡ እንዳልል ፡ እንዳልሰጋበት ፡ ዛሬም
አብሮኝ ፡ አለ ፡ ቤቴ ፡ ባይመቸውም (፪x)

እርሱማ ፡ እየበደልኩት ፡ ቻለኝ
እርሱማ ፡ እየራቅኩት ፡ ቀረበኝ
እርሱማ ፡ ሰለቸኝ ፡ ወዲያ ፡ አላለኝ (፪x)

ብሸሸው ፡ ብርቀው ፡ አለቅ ፡ ያደረገኝ
ጌታ ፡ አይደል ፡ ወይ ፡ ጌታ ፡ አይደለም ፡ ዎይ?!
ከ'ነማንነቴ ፡ የወደደኝ ፡ ጌታ ፡ አይደለም ፡ ዎይ?! (፪x)

እያባበለኝ (፫x)
ተሸከመኝ (፫x)

በምክሩም ፡ ሲያስተምረኝ ፡ ደጉን ፡ ሲያሰየኝ
እንደ ፡ አባት ፡ ሲቀጣኝ
ፍቅር ፡ ማለት ፡ ምን ፡ እንደሆነ ፡ አወኩኝ
መልሶ ፡ ሲያባብለኝ ፡ አለው ፡ ሲለኝ ፡ ሲያበረታታኝ
ፍቅር ፡ ማለት ፡ ምን ፡ እንደሆነ ፡ አወ'ኩኝ (፪x)

እያባበለኝ (፫x)
ተሸከመኝ (፫x)

ቀን ፡ ጠብቆ ፡ ገሸሽ ፡ ይልብኝ ፡ ይሆን ፡ ወይ?
አለልኝ ፡ ስል ፡ ዓይንሽ/ህ ፡ ለአፈር ፡ ይለኛል ፡ ወይ?
ብዬ ፡ እንዳልል ፡ እንዳልሰጋበት ፡ ዛሬም
አብሮኝ ፡ አለ ፡ ቤቴ ፡ ባይመቸውም (፪x)

እርሱማ ፡ እየበደልኩት ፡ ቻለኝ
እርሱማ ፡ እየራቅኩት ፡ ቀረበኝ
እርሱማ ፡ ሰለቸኝ ፡ ወዲያ ፡ አላለኝ (፪x)

ከሞት ፡ አፋፍ ፡ ነጥቆ ፡ ተስፋን ፡ የጨመረልኝ
ጌታ ፡ አይደል ፡ ወይ ፡ ጌታ ፡ አይደለም ፡ ዎይ?!
የተቆረጠውን ፡ የቀጠለልኝ ፡ ጌታ ፡ አይደለም ፡ ዎይ?! (፪x)

እያባበለኝ ፣ እያባበለኝ ፣ እያባበለኝ
ተሸከመኝ ፣ ተሸከመኝ ፣ ተሸከመኝ (፫x)