ኤልራሂም (Elrahim) - ቤተልሔም ፡ ተዘራ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ቤተልሔም ፡ ተዘራ
(Bethlehem Tezera)

Bethlehem Tezera 3.jpg


(3)

ዕድሜዬ ፡ በቤትህ ፡ ይለቅ
(Edmieyie Bebieteh Yileq)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፱ (2007)
ቁጥር (Track):

(7)

ርዝመት (Len.): 4:54
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የቤተልሔም ፡ ተዘራ ፡ አልበሞች
(Albums by Bethlehem Tezera)

የሹዋ ፡ ሮሓሚን
ኤል ፡ ሮሓሚን


አዝ፦ ሲምር ፡ ይምራል ፡ ጌታ
ሳያቅማማ ፡ ለአፍታ
ላያስበው ፡ መልሶ
እንባን ፡ ከዓይን ፡ አብሶ
ይቅር ፡ ይላል ፡ ፈውሶ (፪x)

አላውቀውም ፡ ቢል ፡ ቢምል ፡ ቢክድም
ራሱን ፡ ሊያድን ፡ ራሱን ፡ ቢወድም
መልሶ ፡ ሲያዝን ፡ ሲፀፀት ፡ አየው
የመንግሥቱን ፡ ቁልፍ ፡ በእጁ ፡ አስጨበጠው

ጌታ ፡ ይምራል ፡ ጌታ ፡ ይረሳል
ኃጢአትን ፡ ደግሞ ፡ መቼ ፡ ያስታውሳል
የማረኝ ፡ ነኝ ፡ የተወልኝ
ላያወሳው ፡ ላይደግምብኝ (፪x)

አዝ፦ ሲምር ፡ ይምራል ፡ ጌታ
ሳያቅማማ ፡ ለአፍታ
ላያስበው ፡ መልሶ
እንባን ፡ ከዓይን ፡ አብሶ
ይቅር ፡ ይላል ፡ ፈውሶ (፪x)

ኃጢአት ፡ ቢያደርግም ፡ ምልስ ፡ ልብ ፡ ይዟል
የምህረቱን ፡ ደጅ ፡ ፈጥኖ ፡ ያንኳኳል
የተጻፈልን ፡ ለትምህርት ፡ ነው
ምስክሩ ፡ ግን ፡ እንደ ፡ ልቤ ፡ ነው

ጌታ ፡ ይምራል ፡ ጌታ ፡ ይረሳል
ኃጢአትን ፡ ደግሞ ፡ መቼ ፡ ያስታውሳል
የማረኝ ፡ ነኝ ፡ የተወልኝ
ላያወሳው ፡ ላይደግምብኝ (፪x)

አዝ፦ ሲምር ፡ ይምራል ፡ ጌታ
ሳያቅማማ ፡ ለአፍታ
ላያስበው ፡ መልሶ
እንባን ፡ ከዓይን ፡ አብሶ
ይቅር ፡ ይላል ፡ ፈውሶ (፪x)

ድርሻውን ፡ ወስዶ ፡ ትቶ ፡ ቢወጣ
እንዲያው ፡ ሲባዝን ፡ መቅኖውን ፡ አጣ
ባሪያ ፡ ልሁን ፡ ሲል ፡ ዕድል ፡ ካገኘሁ
የጠበቀው ፡ ግን ፡ ልጅነቱ ፡ ነው

ጌታ ፡ ይምራል ፡ ጌታ ፡ ይረሳል
ኃጢአትን ፡ ደግሞ ፡ መቼ ፡ ያስታውሳል
የማረኝ ፡ ነኝ ፡ የተወልኝ
ላያወሳው ፡ ላይደግምብኝ (፪x)

አዝ፦ ሲምር ፡ ይምራል ፡ ጌታ
ሳያቅማማ ፡ ለአፍታ
ላያስበው ፡ መልሶ
እንባን ፡ ከዓይን ፡ አብሶ
ይቅር ፡ ይላል ፡ ፈውሶ (፪x)

አዶናይ ፡ ሮሆሚን
ራፋዬል ፡ ሮሆሚን
መሲያሕ ፡ ሮሆሚን
ኤል ፡ ሮሆሚን
አዶናይ ፡ ሮሆሚን
የሱዋ ፡ ሮሆሚን