አይበዛብህም (Aybezabehem) - ቤተልሔም ፡ ተዘራ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ቤተልሔም ፡ ተዘራ
(Bethlehem Tezera)

Bethlehem Tezera 1.jpg


(1)

አቤት ፡ አምላኬ
(Abiet Amlakie)

ቁጥር (Track):

(7)

ርዝመት (Len.): 7:12
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የቤተልሔም ፡ ተዘራ ፡ አልበሞች
(Albums by Bethlehem Tezera)

ገንኖ ፡ ገንኖ ፡ ስምህ ፡ መውጣቱ
ፍጥረት ፡ ሁሉ ፡ ስላንተ ፡ ማውራቱ
ከፍታ ፡ ላይ ፡ አለመድረሱ ፡ ይሄ ፡ ሁሉ ፡ ማዕረጉ
ልክ ፡ ነው ፡ አይበዛብህ ፡ እንዲያውም ፡ ስያንስብህ (፫x)

ማን ፡ ብሎህ ፡ ከበርህ ፡ አንተ ፡ እራስህ ፡ ክቡር
ማን ፡ ሾሞህ ፡ ነገስህ ፡ አንተ ፡ እራስህ ፡ ንግስ
ማን ፡ ብሎህ ፡ ክቡር ፡ ሆንክ ፡ ማን ፡ ሾሞህ ፡ ነገሥህ (፪x)

አንተ ፡ እራስህ ፡ ክቡር ፡ ነህ (፪x)
አንተ ፡ እራስህ ፡ ንጉስ ፡ ነህ (፪x)
እራስህ ፡ አንተ ፡ እራስህ ፡ ክቡር ፡ ነህ
እራስህ ፡ አንተ ፡ እራስህ ፡ ንጉሥ ፡ ነህ
  
ጌታዬ ፡ እኔ ፡ ከምልህ ፡ አንተ ፡ ያለህ ፡ ብዙ ፡ ነው
ስለገረመኝ ፡ ብቻ ፡ እንዲህ ፡ ነህ ፡ እልሃለሁ (፪x)

ምስጋናዬን ፡ እሰማለሁ ፡ በከንፈሬ
የወጣው ፡ ግን ፡ የሞላው ፡ ነው ፡ ነው ፡ ከልቤ
አምልኮዬን ፡ እሰማለሁ ፡ በከንፈሬ
የወጣው ፡ ግን ፡ የሞላው ፡ ነው ፡ ከልቤ

ከልቤ ፡ ነው ፡ ከልቤ ፡ አይደለም ፡ በከንፈሬ (፪x)

ዝማሬዬን ፡ አሰማለሁ ፡ በከንፈሬ
የወጣው ፡ ግን ፡ የሞላው ፡ ነው ፡ ከልቤ
አድናቆቴን ፡ አሰማለሁ ፡ በከንፈሬ
የወጣው ፡ ግን ፡ የሞላው ፡ ነው ፡ ከልቤ

ከልቤ ፡ ነው ፡ ከልቤ ፡ አይደለም ፡ በከንፈሬ (፪x)

ክበር ፡ ይላሉ ፡ ንገሥ ፡ ይላሉ
በሰማይ ፡ ያሉ ፡ በምድር ፡ ያሉ
ሲሉህ ፡ ሰምቼ ፡ ልልህ ፡ ቆምኩኝ
እኔም ፡ የራሴ ፡ ምሥጋና ፡ አለኝ (፪x)

አለኝ ፡ ምሥጋና ፡ አለኝ
አለኝ ፡ ዝማሬ ፡ አለኝ
አለኝ ፡ አምልኮ ፡ አለኝ
አለኝ ፡ አድናቆት ፡ አለኝ (፪x)