መድኃኒዓለም (Medhanialem) - በረከት ፡ ተስፋዬ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
በረከት ፡ ተስፋዬ
(Bereket Tesfaye)

Bereket Tesfaye 1.jpeg


(1)

ሊቀ ፡ ካህኔ
(Liqe Kahenie)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ (2007)
ቁጥር (Track):

(2)

ርዝመት (Len.): 5:46
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የበረከት ፡ ተስፋዬ ፡ አልበሞች
(Albums by Bereket Tesfaye)

 
አዝ:- የፍቅር ፡ አምላክ ፡ የሁሉም (፫x)
ደስ ፡ ደስ ፡ ይለኛል
ሥሙን ፡ ስጠራው ፡ የመድኃኒዓለም (፪x)

መድሃኒዓለም ፡ ለዘለዓለም ፡ አይጠገብም ፡ (አሃ) (፪x)
መድሃኒዓለም ፡ አይጠገብም
የእኔ ፡ ኢየሱስ ፡ ዘለዓለም ፡ ንገሥ (፪x)

አሃሃ ፡ ኢየሱስ (፪x) ፡ ኢየሱስ ፡ የምለው
ምህረት ፡ ተደርጐልኝ ፡ ቆሜ ፡ መሄዴ ፡ ነው

ሞኝ ፡ ሆኜ ፡ አይደለም ፡ ወይም ፡ ተታልዬ
ኢየሱስ ፡ የምለው ፡ ሁሉን ፡ ነገር ፡ ጥዬ
ገብቶብኝ ፡ ነው ፡ እንጂ ፡ ታላቁ ፡ ፍቅር
ደቀ ፡ መዝሙር ፡ ሆንኩኝ ፡ ሳላንገራግር

አሸንፎኝ ፡ በፍቅር ፡ አደረገኝ ፡ ደቀ ፡ መዝሙር (፪x)
ከፍቶልኝ ፡ ትልቁን ፡ በር ፡ አደረገኝ ፡ ደቀ ፡ መዝሙር(፪x)

አሃሃ ፡ የድሃ ፡ አደግ ፡ አባት
የመበለት ፡ ዳኛ
ቅንነት ፡ ያለበት ፡ ሁልጊዜ ፡ እውነተኛ

ቢፈለግ ፡ ቢፈለግ ፡ ዓለምም ፡ ቢዞር
አንድም ፡ አይገኝም ፡ እንደእግዚአብሄር
የምስኪን ፡ ጓደኛ ፡ መልካሙ ፡ እረኛ ፡ ኢየሱስ ፡ አለልኛ
ታማኝ ፡ ባልንጀራ ፡ ኢየሱስ ፡ አለልኛ

የምስኪን ፡ ጓደኛ ፡ መልካሙ ፡ እረኛ ፡ ኢየሱስ ፡ አለልኛ
የድሃ ፡ አደግ ፡ አባት ፡ የመበለት ፡ ዳኛ ፡ ኢየሱስ ፡ አለልኛ
የምስኪን ፡ ጓደኛ ፡ መልካሙ ፡ እረኛ
ታማኝ ፡ ባልንጀራ ፡ ኢየሱስ ፡ አለልኛ
የድሃ ፡ አደግ ፡ አባት ፡ የመበለት ፡ ዳኛ
ቅንነት ፡ ያለበት ፡ ሁልጊዜ ፡ እውነተኛ

አዝ:- የፍቅር ፡ አምላክ ፡ የሁሉም (፫x)
ደስ ፡ ደስ ፡ ይለኛል
ሥሙን ፡ ስጠራው ፡ የመድኃኒዓለም (፪x)

መድሃኒዓለም ፡ ለዘለዓለም ፡ አይጠገብም ፡ (አሃ) (፪x)
መድሃኒዓለም ፡ አይጠገብም
የእኔ ፡ ኢየሱስ ፡ ዘለዓለም ፡ ንገሥ (፪x)

አሃሃ ፡ ቸሩ ፡ መድሃኒዓለም ፡ የዓለም ፡ መድሃኒት
ለእኛ ፡ የደረሰ ፡ በአስጨናቂው ፡ ሌሊት

ሥሙ ፡ ይታወጅ ፡ በአገሬ ፡ ላይ
የኢትዮጵያ ፡ አምላክ ፡ እርሱ ፡ አይደለም ፡ ወይ
ዘንዶውንም ፡ ወጋ ፡ ረሃብን ፡ ቆራረጠ
ለሃገሬ ፡ ልጆች ፡ ምግባቸውን ፡ ሰጠ

የኢትዮጵያ ፡ አምላክ (፪x) ፡ ሥምህ ፡ ይባረክ (፪x)
የኢትዮጵያ ፡ አምላክ ፡ ሥምህ ፡ ይባረክ
የእኛ ፡ አምላክ ፡ ሥምህ ፡ ይባረክ
የኢትዮጵያ ፡ አምላክ ፡ ሥምህ ፡ ይባረክ
የእስራኤል ፡ አምላክ ፡ ሥምህ ፡ ይባረክ