ከሚጠፉት (Kemitefut) - በረከት ፡ ተስፋዬ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
በረከት ፡ ተስፋዬ
(Bereket Tesfaye)

Bereket Tesfaye 1.jpeg


(1)

ሊቀ ፡ ካህኔ
(Liqe Kahenie)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ (2007)
ቁጥር (Track):

(4)

ርዝመት (Len.): 5:01
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የበረከት ፡ ተስፋዬ ፡ አልበሞች
(Albums by Bereket Tesfaye)

በዓለም ፡ ፍቅር ፡ እንዳልነደፍ
ከሚጠፉት ፡ ጋር ፡ እንዳልሰለፍ
አረማመዴን ፡ አቅናውና
የራስህ ፡ አድርገኝ ፡ ቀይረኝና

ከሚጠፉት ፡ እንዳልሆን ፡ ጠብቀኝ::
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ምህረትህን ፡ አብዛልኝ (፪x)

አንተ ፡ የሌለህበት
የዓለም ፡ ዝና ፡ የዓለም ፡ ዕውቀት
ኢሄ ፡ ሁሉ ፡ ከንቱ ፡ ነዉ
ንፋስን ፡ እንደመከተል ፡ ነው

ከሚጠፉት ፡ እንዳልሆን ፡ ጠብቀኝ::
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ምህረትህን ፡ አብዛልኝ (፪x)

በአንደበቴ ፡ እንዳልረክስ
ወንድሜንም ፡ እንዳልተነኩስ
አቤቱ ፡ ማስተዋልን ፡ ስጠኝ
መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ና ፡ አስተምረኝ

ከሚጠፉት ፡ እንዳልሆን ፡ ጠብቀኝ::
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ምህረትህን ፡ አብዛልኝ (፪x)

ዓይኔን ፡ ወደ ፡ አንተ ፡ እንዳቀና
መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ናልኝና
ፈውሰኝ ፡ ቀድሰኝ
መጠቀሚያ ፡ ገንዘብህ ፡ አድርገኝ

ከሚጠፉት ፡ እንዳልሆን ፡ ጠብቀኝ::
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ምህረትህን ፡ አብዛልኝ (፪x)