የነፍስ ፡ አባቴ (Yenefs Abatie) - አዜብ ፡ መለሰ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዜብ ፡ መለሰ
(Azeb Melesse)

Azeb Melesse 1.jpeg


(1)

የነፍስ ፡ አባቴ
(Yenefs Abatie)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬ (2011)
ቁጥር (Track):

፲ ፩ (11)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዜብ ፡ መለሰ ፡ አልበሞች
(Albums by Azeb Melesse)

 
አዝ:- ዋስ ፡ ጠበቃዬ (፪x) ፡ ካህኔ
ኢየሱስ ፡ የነፍስ ፡ አባቴ (፬x)

የእርግብ ፡ የፍየል ፡ ደም ፡ ይፍሰስ
መሰዊያ ፡ ላድርጋቸው ፡ እንድዱት
የህዝቡ ፡ ኀጢአት ፡ እንዲሰረይለት
ሚቃጠል ፡ መስዋዕት ፡ ይቅረብለት
ይህ ፡ ስርአት ፡ ቀረ (፬x)
መስዋዕቴ ፡ ኢየሱስ ፡ ሆነ
መስዋዕቴ ፡ የከበረ
(፪x)

አዝ:- ዋስ ፡ ጠበቃዬ (፪x) ፡ ካህኔ
ኢየሱስ ፡ የነፍስ ፡ አባቴ (፬x)

ኀጢአትን ፡ ማስወገድ ፡ የማይችሉ
መስዋዕት ፡ ሁልጊዜ ፡ ሲያቅርቡ
እርሱ ፡ ግን ፡ ለአንዴ ፡ ፈጽሞ
ቀደሰኝ ፡ እራሱን ፡ አቅርቦ
የአዲስ ፡ ኪዳን ፡ ልጅ ፡ ነኝ (፬x)
የተሻለ ፡ ካህን ፡ አለኝ
የተሻለ ፡ ኪዳን ፡ አለኝ
(፪x)

አዝ:- ዋስ ፡ ጠበቃዬ (፪x) ፡ ካህኔ
ኢየሱስ ፡ የነፍስ ፡ አባቴ (፬x)

ቃልኪዳን ፡ ከእኔ ፡ ጋር ፡ አደረገ
ህጉንም ፡ በልቤ ፡ አስቀመጠ
በአዲስና ፡ በሕያው ፡ መንገድ
አስገባኝ ፡ በስጋው ፡ በደም
የአዲስ ፡ ኪዳን ፡ ልጅ ፡ ነኝ (፬x)
የተሻለ ፡ ካህን ፡ አለኝ
የተሻለ ፡ ኪዳን ፡ አለኝ
(፪x)

አዝ:- ዋስ ፡ ጠበቃዬ (፪x) ፡ ካህኔ
ኢየሱስ ፡ የነፍስ ፡ አባቴ (፬x)

እግዚአብሔር ፡ የራሱን ፡ ፍቅር ፡ የገለጠበት
ስጦታው ፡ እንዴት ፡ ካለ ፡ ሞት ፡ እኔን ፡ ያዳነበት
ተአምር ፡ የምለው ፡ በሕይወቴ
ኢየሱሴ ፡ የነፍስ ፡ አባቴ
ኦ ፡ ኢየሱሴ ፡ የነፍስ ፡ አባቴ
(፪x)

የውስጤን ፡ ሁሉ ፡ ማሳየው ፡ ሚስጥረኛዬ
በአብ ፡ ቀኝ ፡ የሚቆምልኝ ፡ ጠበቃዬ
ሚረዳኝ ፡ ደግሞም ፡ ሚረዳኝ ፡ ሊቀ ፡ ካህኔ
ኢየሱሴ ፡ የነፍስ ፡ አባቴ
ኦ ፡ ኢየሱሴ ፡ የነፍስ ፡ አባቴ
(፮x)