ከሁኔታ ፡ በላይ (Kehunieta Belay) - አዜብ ፡ መለሰ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዜብ ፡ መለሰ
(Azeb Melesse)

Azeb Melesse 1.jpeg


(1)

የነፍስ ፡ አባቴ
(Yenefs Abatie)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬ (2011)
ቁጥር (Track):

(5)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዜብ ፡ መለሰ ፡ አልበሞች
(Albums by Azeb Melesse)

 
አዝ:- ከሁኔታ ፡ በላይ ፡ ጌታ ፡ የበላይ (፪x) (ጌታ ፡ የበላይ (፪x))
ከእኔ ፡ ችግር ፡ በላይ ፡ ጌታ ፡ የበላይ (፪x) (ጌታ ፡ የበላይ (፪x))

ብዙ ፡ ጥያቄ ፡ እንቆቅልሽ ፡ እያለኝ
ግን ፡ እዘምራለሁ ፡ ሁሌ ፡ ደስተኛ ፡ ነኝ
ለእኔ ፡ የተከፈለው ፡ ትልቅ ፡ የደም ፡ ዋጋ
አይመጣጠንም ፡ ከሁኔታዬ ፡ ጋር

አዝ:- እንቆቅልሼ ፡ እያለ
ችግር ፡ መከራ ፡ እያለ
ግን ፡ እዘምራለሁ ፡ ድል ፡ አለ
ግን ፡ እዘምራለሁ ፡ መልስ ፡ አለ (፪x)
ከሁኔታ ፡ በላይ ፡ ጌታ ፡ የበላይ (፪x) (ጌታ ፡ የበላይ (፪x))
ከእኔ ፡ ችግር ፡ በላይ ፡ ጌታ ፡ የበላይ (፪x) (ጌታ ፡ የበላይ (፪x))

በእንግድነት ፡ አገር ፡ ለጊዜው ፡ ምኖረው
በምታልፈው ፡ ዓለም ፡ ትቼው ፡ ለምሄደው
ቢሞላ ፡ ባይሞላ ፡ እኔ ፡ ምን ፡ ቸገረኝ
ስሄድ ፡ ምገባበት ፡ በሰማይ ፡ ቤት ፡ አለኝ

አዝ:- እንቆቅልሼ ፡ እያለ
ችግር ፡ መከራ ፡ እያለ
ግን ፡ እዘምራለሁ ፡ ድል ፡ አለ
ግን ፡ እዘምራለሁ ፡ መልስ ፡ አለ (፪x)
ከሁኔታ ፡ በላይ ፡ ጌታ ፡ የበላይ (፪x) (ጌታ ፡ የበላይ (፪x))
ከእኔ ፡ ችግር ፡ በላይ ፡ ጌታ ፡ የበላይ (፪x) (ጌታ ፡ የበላይ (፪x))

እንዳላጉረመርም ፡ አፌን ፡ በምሥጋና
ሃዘንተኛ ፡ እንዳልመስል ፡ ፊቴ ፡ እያበራ
ኢሄ ፡ እንዴት ፡ ሆነ ፡ ለምትጠይቁኝ
ሁሉን ፡ የሚያስረሳ ፡ አባት ፡ ስላለኝ

አዝ:- እንቆቅልሼ ፡ እያለ
ችግር ፡ መከራ ፡ እያለ
ግን ፡ እዘምራለሁ ፡ ድል ፡ አለ
ግን ፡ እዘምራለሁ ፡ መልስ ፡ አለ (፪x)
ከሁኔታ ፡ በላይ ፡ ጌታ ፡ የበላይ (፪x) (ጌታ ፡ የበላይ (፪x))
ከእኔ ፡ ችግር ፡ በላይ ፡ ጌታ ፡ የበላይ (፪x) (ጌታ ፡ የበላይ (፪x))