ኢትዮጵያ (Ethiopia) - አዜብ ፡ መለሰ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዜብ ፡ መለሰ
(Azeb Melesse)

Azeb Melesse 1.jpeg


(1)

የነፍስ ፡ አባቴ
(Yenefs Abatie)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬ (2011)
ቁጥር (Track):

፲ ፫ (13)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዜብ ፡ መለሰ ፡ አልበሞች
(Albums by Azeb Melesse)

 
ኢትዮጵያ (፬x)

ስንጮህ ፡ ስናለቅስ ፡ ሳይሰማው ፡ ቀርቶ
አይደል ፡ ላለማገዝ ፡ ላለመርዳት ፡ ብሎ
አሁን ፡ ምናየውን ፡ ዳግም ፡ እንዳናየው
እስከመጨረሻ ፡ ሊቀብረን ፡ ሊያስቀረን

አዝ:- ኢትዮጵያ ፡ መከራሽ ፡ እንደዚህ ፡ የበዛው
ጨለማው ፡ እንዲህ ፡ የበረታው
የኢየሱሴ ፡ ስራ ፡ ይገለጥ ፡ ዘንድ ፡ ነው
ስለ ፡ እግዚአብሔር ፡ ክብር ፡ ነው ፡ እንጂ
ልትጠፊ ፡ አይደለም ፡ ልትዋረጂ

ኢትዮጵያ (፬x)

ዛሬ ፡ የሚቀመስ ፡ ምንም ፡ ነገር ፡ ሳይኖር
ነገ ፡ ይጠገባል ፡ ተርፎ ፡ ይሸጣል ፡ ቢለን
የችግሩ ፡ ብዛት ፡ ግራ ፡ ቢያጋባንም
ቃል ፡ ወጥቷል ፡ ከሰማይ ፡ መሆኑ ፡ አይቀርም

አዝ:- ኢትዮጵያ ፡ መከራሽ ፡ እንደዚህ ፡ የበዛው
ጨለማው ፡ እንዲህ ፡ የበረታው
የኢየሱሴ ፡ ስራ ፡ ይገለጥ ፡ ዘንድ ፡ ነው
ስለ ፡ እግዚአብሔር ፡ ክብር ፡ ነው ፡ እንጂ
ልትጠፊ ፡ አይደለም ፡ ልትዋረጂ

ሰው ፡ ደመናን ፡ አይቶ ፡ ሊዘንብ ፡ ነው ፡ ይላል
አምላኬ ፡ በራሱ ፡ ተማምኖ ፡ ያወራል
ተስፋ ፡ ገብቶላታል ፡ ላለሁባት ፡ ምድሬ
እኔ ፡ እርግጠኛ ፡ ነኝ ፡ ታየዋልች ፡ ህልሜን

አዝ:- ኢትዮጵያ ፡ መከራሽ ፡ እንደዚህ ፡ የበዛው
ጨለማው ፡ እንዲህ ፡ የበረታው
የኢየሱሴ ፡ ስራ ፡ ይገለጥ ፡ ዘንድ ፡ ነው
ስለ ፡ እግዚአብሔር ፡ ክብር ፡ ነው ፡ እንጂ
ልትጠፊ ፡ አይደለም ፡ ልትዋረጂ

የኢትዮጵያን ፡ መባረክ ፡ አትጠራጠሩ
ይሄ ፡ በተአምር ፡ አይሆንም ፡ አትበሉ
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ ሆነ ፡ ነው ፡ በቃሉ
እርሱ ፡ እውነተኛ ፡ አይዋሽም ፡ እመኑ

አዝ:- ኢትዮጵያ ፡ መከራሽ ፡ እንደዚህ ፡ የበዛው
ጨለማው ፡ እንዲህ ፡ የበረታው
የኢየሱሴ ፡ ስራ ፡ ይገለጥ ፡ ዘንድ ፡ ነው
ስለ ፡ እግዚአብሔር ፡ ክብር ፡ ነው ፡ እንጂ
ልትጠፊ ፡ አይደለም ፡ ልትዋረጂ

ኢትዮጵያ (፬x)