አልከዳውም (Alkedawem) - አዜብ ፡ መለሰ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዜብ ፡ መለሰ
(Azeb Melesse)

Azeb Melesse 1.jpeg


(1)

የነፍስ ፡ አባቴ
(Yenefs Abatie)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬ (2011)
ቁጥር (Track):

(7)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዜብ ፡ መለሰ ፡ አልበሞች
(Albums by Azeb Melesse)

 
አዝ:- አንዳንዱ ፡ ንዋይ ፡ ፈልጐ
ይሄዳል ፡ አምላኩን ፡ ትቶ
ለሚያልፈው ፡ ለሚጠፋው
ይሄ ፡ ሰው ፡ እንዴት ፡ ሞኝ ፡ ነው

ተራራ ፡ ሕይወት ፡ ዳገት ፡ ነው/መከራ ፡ ሕይወት ፡ ሰልፍ ፡ ነው
ለመኖር ፡ ሁሌ ፡ ትግል ፡ ነው
ቢሆንም ፡ ለተድላ ፡ ብዬ
አልሄድም ፡ አማላኬን ፡ ጥዬ (፪x)

አዝ:- አንዳንዱ ፡ ንዋይ ፡ ፈልጐ
ይሄዳል ፡ አምላኩን ፡ ትቶ
ለሚያልፈው ፡ ለሚጠፋው
ይሄ ፡ ሰው ፡ እንዴት ፡ ሞኝ ፡ ነው

ሌሊት ፡ ላይ ፡ ፀሐይ ፡ እንድትወጣ
ብፈልግ ፡ መች ፡ ይሆንና
ለሁሉም ፡ ስርአት ፡ አለው
እንስኪነጋ ፡ እጠብቃለሁ (፪x)

አዝ:- አንዳንዱ ፡ ንዋይ ፡ ፈልጐ
ይሄዳል ፡ አምላኩን ፡ ትቶ
ለሚያልፈው ፡ ለሚጠፋው
ይሄ ፡ ሰው ፡ እንዴት ፡ ሞኝ ፡ ነው

እግዚአብሔር ፡ ለእኔ ፡ ያስቀመጠውን
ለማንም ፡ እንደማይሰጠው
ገብቶናል ፡ ተረድቻለሁ
እርሱን ፡ ትቼ ፡ የት ፡ እሄዳለሁ (፪x)

አዝ:- አንዳንዱ ፡ ንዋይ ፡ ፈልጐ
ይሄዳል ፡ አምላኩን ፡ ትቶ
ለሚያልፈው ፡ ለሚጠፋው
ይሄ ፡ ሰው ፡ እንዴት ፡ ሞኝ ፡ ነው

አልከዳውም ፡ ይሄን ፡ ሳወራ
ሞራልም ፡ አይደል ፡ ፉከራ
ከልቤ ፡ እወደዋለው
ያለ ፡ እርሱ ፡ እንዴት ፡ እኖራለሁ (፪x)

አዝ:- አንዳንዱ ፡ ንዋይ ፡ ፈልጐ
ይሄዳል ፡ አምላኩን ፡ ትቶ
ለሚያልፈው ፡ ለሚጠፋው
ይሄ ፡ ሰው ፡ እንዴት ፡ ሞኝ ፡ ነው