የተፈታው ፡ እስራቴ (Yetefetaw Eseratie) - አዜብ ፡ ኃይሉ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዜብ ፡ ኃይሉ
(Azeb Hailu)

Lyrics.jpg


(4)

እንታረቅ
(Enetareq)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬(2011)
ቁጥር (Track):

(8)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዜብ ፡ ኃይሉ ፡ አልበሞች
(Albums by Azeb Hailu)

 
የታሰረችው ፡ ውርንጭላ ፡ ለኢየሱስ ፡ መቀመጫ
ታስፈልገዋለችና ፡ አምጧት ፡ በፍጥነት/በቶሎ ፡ ፍቱና
(፪x)
ለምን ፡ ቢባል ፡ ሊከብርባት ፣ ለምን ፡ ቢባል ፡ ሊነግስባት
እራሱን ፡ በላዯ ፡ አድርጐ ፡ ኢየሩሳሌም ፡ ሊገባባት/ሊጓዝባት (፪x)

አዝ፦ የተፈታው ፡ እስራቴ ፡ የታወጀው ፡ አርነቴ
በቀራንዮ ፡ በጐልጐታ ፡ እራሱን ፡ ሲሰጥ ፡ ለእኔ ፡ ጌታ
ተፈጸመ ፡ ሲል ፡ ሲናገር ፡ የተጫነኝ ፡ ክፉ ፡ ቀንበር
ሲወድቅ ፡ አየሁ ፡ ሲሰባበር ፡ ይሁን ፡ ለእርሱ ፡ ብዙ ፡ ክብር

በድቅድቁ ፡ ጨለማ ፡ ተጥዬ ፡ ስደናበር
በጠበቀው ፡ ሰንሰለት ፡ ባማይፈታው ፡ እስር
እንድጠፋ ፡ ለሲዖል ፡ የታጨሁ ፡ በመሆኔ
በግፍ ፡ ነፍሴ ፡ ሊሰዋ ፡ ሊታረድ ፡ በጭካኔ
አዋጅ ፡ ወጣ ፡ ከሰማይ ፡ ከዙፋን ፡ ከመቅደሱ
ፍቷትና ፡ ትለቀቅ ፡ ተባለ ፡ ክብር ፡ ለእርሱ
አገኛታለሁ ፡ ብሎ ፡ የጐመጀው ፡ ጠላቴ
እፍረት ፡ ተከናነበ ፡ እኔም ፡ ጸና ፡ ጉልበቴ

አዝ፦ የተፈታው ፡ እስራቴ ፡ የታወጀው ፡ አርነቴ
በቀራንዮ ፡ በጐልጐታ ፡ እራሱን ፡ ሲሰጥ ፡ ለእኔ ፡ ጌታ
ተፈጸመ ፡ ሲል ፡ ሲናገር ፡ የተጫነኝ ፡ ክፉ ፡ ቀንበር
ሲወድቅ ፡ አየሁ ፡ ሲሰባበር ፡ ይሁን ፡ ለእርሱ ፡ ብዙ ፡ ክብር

አጥምዶብኝ ፡ ወጥመዱን ፡ እግሮቼ ፡ ስር ፡ ዘርግቶ
መረብ ፡ ውስጥ ፡ እንድገባ ፡ ፈልጐ ፡ እጅግ ፡ ጓጉቶ
መስሎት ፡ የተሳካለት ፡ የገባሁ ፡ በመዳፉ
ደስ ፡ ብሎት ፡ ጨፈረ ፡ ሊውጠኝ ፡ ይዞ ፡ በአፉ
የይሁዳው ፡ አንበሳ ፡ የቀራንዮ ፡ ጀግና
ጉልበተኛው ፡ ኢየሱስ ፡ ስመጥሩ ፡ ገናና
ፍፁም ፡ አይሆንም ፡ ብሎ ፡ ከሰማያት ፡ ወረደ
እራሱን ፡ ስለእኔ ፡ ሲሰጥ ፡ ጠላቴ ፡ ተዋረደ

አዝ፦ የተፈታው ፡ እስራቴ ፡ የታወጀው ፡ አርነቴ
በቀራንዮ ፡ በጐልጐታ ፡ እራሱን ፡ ሲሰጥ ፡ ለእኔ ፡ ጌታ
ተፈጸመ ፡ ሲል ፡ ሲናገር ፡ የተጫነኝ ፡ ክፉ ፡ ቀንበር
ሲወድቅ ፡ አየሁ ፡ ሲሰባበር ፡ ይሁን ፡ ለእርሱ ፡ ብዙ ፡ ክብር

ወገኖች ፡ የምስራች ፡ ተሸንፏል ፡ ዲያቢሎስ
የሞትን ፡ ጣር ፡ ባጠፋው ፡ በእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ በኢየሱስ
ከመስቀሉ ፡ ስር ፡ ያኔ ፡ አድቅቆታል ፡ ቀጥቅጦ
ለሚያምኑበት ፡ በሙሉ ፡ አስገዝቶታል ፡ ረግጦ
ወጥመዱ ፡ ተሰበረ ፡ ነፍሴ ፡ እንደወፍ ፡ በረረች
ሰይጣን ፡ ባዶ ፡ እጁን ፡ ቀረ ፡ ከግዞቱ ፡ አመለጠች
ሞትስ ፡ መውጊያው ፡ የታለ ፡ ጌታ ፡ ሞቶ ፡ ተነሳ
ከሲዖል ፡ ምርኮን ፡ ማርኮ ፡ በስልጣኑ ፡ ድል ፡ ነሳ

አዝ፦ የተፈታው ፡ እስራቴ ፡ የታወጀው ፡ አርነቴ
በቀራንዮ ፡ በጐልጐታ ፡ እራሱን ፡ ሲሰጥ ፡ ለእኔ ፡ ጌታ
ተፈጸመ ፡ ሲል ፡ ሲናገር ፡ የተጫነኝ ፡ ክፉ ፡ ቀንበር
ሲወድቅ ፡ አየሁ ፡ ሲሰባበር ፡ ይሁን ፡ ለእርሱ ፡ ብዙ ፡ ክብር (፪x)