አንተ ገናና ነህ (Ante Genana Neh) - አዜብ ፡ ኃይሉ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዜብ ፡ ኃይሉ
(Azeb Hailu)

Lyrics.jpg


(4)

እንታረቅ
(Enetareq)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬ (2011)
ቁጥር (Track):

(1)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዜብ ፡ ኃይሉ ፡ አልበሞች
(Albums by Azeb Hailu)

ላሞግሰው ፡ ዙፋንህን ፡ ላደናንቅ
ከእግሮችህ ፡ ስር ፡ ሆኜ ፡ ቅኔን ፡ ላፈልቅ
አንደበቴን ፡ ቀድሼ ፡ ዜማ ፡ ላፈስ
ጌታ ፡ ልልህ ፡ መጣሁ ፡ ክበር ፡ ንገሥ

እንዲህ ፡ ከሚሉ ፡ ጋራ ፡ ልተባበር
እኔም ፡ የእራሴን ፡ ፈንታ ፡ ልጨምርልህ
ይሄም ፡ ትንሽ ፡ ነው ፡ ለአንተ ፡ አይበዛምና
ከናፍርቶቼ ፡ ይጥሩህ ፡ ብለው ፡ ገናና ፡ አንተ ፡ ገናና
አንተ ፡ ገናና ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ ገናና (፪x)

በላይ ፡ ነህ ፡ ከዚህም ፡ በላይ ፡ ነህ
በላይ ፡ ነህ ፡ ከዚያም ፡ በላይ ፡ ነህ (፪x)

ከሰማነው ፡ እና ፡ ካየነው
በላይ ፡ ነህ ፡ ከዚህም ፡ በላይ ፡ ነህ
ከዘመርነው ፡ ከሰበክነው
በላይ ፡ ነህ ፡ ከዚያም ፡ በላይ ፡ ነህ (፪x)

የለም (፫x) ፡ ሌላ ፡ ጌታ ፡ የለም
የለም(፫x) ፡ ሌላ ፡ ንጉሥ ፡ የለም
የለም (፫x) ፡ ሌላ ፡ አዳኝ ፡ የለም
የለም (፫x) ፡ ሌላ ፡ ገዢ ፡ የለም
ሌላ ፡ ጌታ ፡ የለም ፣ ሌላ ፡ ንጉሥ ፡ የለም
ሌላ ፡ አዳኝ ፡ የለም ፣ ሌላ ፡ ገዢ ፡ የለም
(፪x)

በእውነትና ፡ በመንፍስ ፡ ስትመለክ
ፍጥረት ፡ ሁሉ ፡ በፊትህ ፡ ሲል ፡ ዝቅ ፡ ዝቅ
ቋንቋው ፡ ሁሉ ፡ ስለአንተ ፡ ዝና ፡ ሲያወራ
ሲባል ፡ ከአማልክት ፡ ሁሉ ፡ ነህ ፡ የተፈራህ

እንዲህ ፡ ከሚሉ ፡ ጋራ ፡ ልተባበር
እኔም ፡ የእራሴን ፡ ፈንታ ፡ ልጨምርልህ
ይሄም ፡ ትንሽ ፡ ነው ፡ ለአንተ ፡ አይበዛምና
ገና ፡ ፍጥሮችህ ፡ ይጥሩህ ፡ ብለው ፡ ገናና ፡ አንተ ፡ ገናና
አንተ ፡ ገናና ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ ገናና (፪x)

በላይ ፡ በሰማይ ፡ ላለው ፡ በዙፋኑ
ለሚገዙለት ፡ እልፍ ፡ ቅዱሳኑ
ለሚባርኩ ፡ ስሙን ፡ በዝማሬ
አምላክ ፡ ለሆነው ፡ ጥንትም ፡ ቢሆን ፡ ዛሬ (፪x)

እኔም ፡ አለኝ ፡ አምልኮ
እኔም ፡ አለኝ ፡ ምሥጋና
እኔም ፡ አለኝ ፡ ዕልልታ
በአመታት ፡ መካከል
ጸንቶ ፡ ለሚኖረው
ለጌቶቹ ፡ ጌታ (፪x)

ለጌቶቹ ፡ ጌታ
ለነገሥታት ፡ ንጉሥ
ለጌቶቹ ፡ ጌታ (፪x)