ክቡር (Kebur) - አዜብ ፡ ኃይሉ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዜብ ፡ ኃይሉ
(Azeb Hailu)

Lyrics.jpg


(4)

እንታረቅ
(Enetareq)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬(2011)
ቁጥር (Track):

(10)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዜብ ፡ ኃይሉ ፡ አልበሞች
(Albums by Azeb Hailu)

 
ከቶ ፡ አልደከመም ፡ ጉልበቱ
ከቶም ፡ አልደነዘም ፡ ስለቱ
ዛሬም ፡ አልፈዘዘም ፡ ውበቱ
ይገርማል ፡ የቃልህ ፡ ጽናቱ

አሁንም ፡ ይሰራል ፡ ያው ፡ ነው
በፍጥረት ፡ ሁሉ ፡ ላይ ፡ ገዢ ፡ ነው
ሰማያት ፡ ቢያልፉም ፡ ምድር
ቃልህ ፡ ለዘለዓለም ፡ ክቡር

አዝክቡር (፫x) ፡ ቃሉ ፡ የእግዚአብሔር
ክቡር (፫x) ፡ ድምጹ ፡ የእግዚአብሔር
ክቡር (፫x) ፡ የእርሱ ፡ ንግግር

ድምጹ ፡ ተራራውን ፡ ያቀልጣል
ጠንካራውን ፡ ዝግባ ፡ ይቆርጣል
ጥቅጥቅ ፡ ያለውን ፡ ጫካ ፡ ይገልጣል
ጌታዬ ሆይ ድምጽህ ያስፈራል

ቃልህ ፡ ሰማያትን ፡ አጽንቷል
ምድርን ፡ ደግሞ ፡ መስርቷል
ሕያውን ፡ ግዑዙንም ፡ ሰርቷል
በዘለዓለም ፡ ክብሩ ፡ ይኖራል

አዝክቡር (፫x) ፡ ቃሉ ፡ የእግዚአብሔር
ክቡር (፫x) ፡ ድምጹ ፡ የእግዚአብሔር
ክቡር (፫x) ፡ የእርሱ ፡ ንግግር

ወጀብ ፡ ነው ፡ ወይ ፡ አውሎ ፡ ንፋሱ
ሰምቶ ፡ መልስ ፡ ያልሰጠው ፡ ለድምጹ
ግዑዝ ፡ ነው ፡ ወይ ፡ ሕያው ፡ ፍጥረት
ሰምተው ፡ ማይታዘዙት

በሰማያት ፡ ያሉ ፡ በምድር
ይገዛሉ ፡ ለእግዚአብሔር
በሁሉ ፡ ላይ ፡ ብርቱ ፡ ገናና
የእኔ ፡ ጌታ ፡ ብቻ ፡ ነውና

ከቶ ፡ አልደከመም ፡ ጉልበቱ
ከቶም ፡ አልደነዘም ፡ ስለቱ
ዛሬም ፡ አልፈዘዘም ፡ ውበቱ
ይገርማል ፡ የቃልህ ፡ ጽናቱ

አሁንም ፡ ይሰራል ፡ ያው ፡ ነው
በፍጥረት ፡ ሁሉ ፡ ላይ ፡ ገዢ ፡ ነው
ሰማያት ፡ ቢያልፉም ፡ ምድርም
ቃልህ ፡ ለዘለዓለም ፡ ክቡር

አዝክቡር (፫x) ፡ ቃሉ ፡ የእግዚአብሔር
ክቡር (፫x) ፡ ድምጹ ፡ የእግዚአብሔር
ክቡር (፫x) ፡ የእርሱ ፡ ንግግር