የማይደክም የማያረጅ (Yemaydekm Yemayareg) - አዜብ ፡ ኃይሉ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዜብ ፡ ኃይሉ
(Azeb Hailu)

Lyrics.jpg


(4)

እንታረቅ
(Enetareq)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬ (2011)
ቁጥር (Track):

(3)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዜብ ፡ ኃይሉ ፡ አልበሞች
(Albums by Azeb Hailu)

የማይደክም ፡ የማያረጅ ፡ ግሩም ፡ አምላክ ፡ ፍፁም ፡ ወዳጅ
ማይሸነፍ ፡ የማይረታ ፡ እርሱ ፡ ብቻውን ፡ ሁሌ ፡ ጌታ (፪x)

በሌሊቱ ፡ በአራተኛው ፡ ክፍል
በሌሊቱ ፡ እጅግ ፡ በከበደው
በሌሊቱ ፡ ታንኳዬም ፡ ሲጨነቅ
በሌሊቱ ፡ ማዕበሉ ፡ ሲገፋው
በሌሊቱ ፡ ድንገት ፡ ከተፍ ፡ አለ
በሌሊቱ ፡ ተገለጠ ፡ ጌታ
በሌሊቱ ፡ የሚያንገላታኝን
በሌሊቱ ፡ ሊገስጽ ፡ ሊመታ

የእኔ ፡ ጌታ ፡ አሃሃሃሃ ፡ የእኔ ፡ ተስፋ
የእኔ ፡ ክብር ፡ ኢየሱስ ፡ የእኔ ፡ አለኝታ (፪x)

አትፍሪ ፡ እኔ ፡ ነኝ ፡ እያለ ፡ የሚያበረታኝን
እንደጌታዬ ፡ እንደኢየሱስ ፡ ከወዴት ፡ ላግኝ
በለመለመው ፡ መስክ ፡ ሚመራኝ ፡ በእረፍት ፡ ውኃ ዘንድ
አላገኝም ፡ በየትም ፡ ስፍራ ፡ እኔን ፡ የሚወድ

ይህ ፡ ነው ፡ አይባልም ፡ ብርታቱ
ሊያድን ፡ ፈጥኖ ፡ ደራሽነቱን
ጠበቃዬ ፡ ነው ፡ በጽድቅ ፡ ፍርዱ
እውነት ፡ ነው ፡ እርምጃው ፡ መንገዱ
ሁሉን ፡ ቻይ ፡ ክንዱን ፡ ዘርግቶ
አቁሞኛል ፡ ከታች ፡ አንስቶ
የማዳኑን ፡ ብርታት ፡ ኃይሉን
ዘምራለሁ ፡ በሌት ፡ በቀን

የማይደክም ፡ የማያረጅ ፡ ግሩም ፡ አምላክ ፡ ፍፁም ፡ ወዳጅ
ማይሸነፍ ፡ የማይረታ ፡ እርሱ ፡ ብቻውን ፡ ሁሌ ፡ ጌታ (፪x)

ብሏልና ፡ እናንተ ፡ ደካሞች
ኑ ፡ ወደ ፡ እኔ ፡ ከነ ፡ ሸክማችሁ
ስጡኝና ፡ የከበዳችሁን
እፎይ ፡ በሉ ፡ እስቲ ፡ ላሳርፋችሁ
እንደቃሉ ፡ የሚያስጨንቀኝን
ስተውለት ፡ ስሰጠው ፡ ነገሬን
የማላውቀው ፡ ሰላም ፡ ወረደብኝ
እፎይ ፡ አልኩኝ ፡ ረሳሁት ፡ ችግሬን

የእኔ ፡ ጌታ ፡ አሃሃሃሃ ፡ የእኔ ፡ ተስፋ
የእኔ ፡ ክብር ፡ ኢየሱስ ፡ የእኔ ፡ አለኝታ (፪x)

አትፍሪ ፡ እኔ ፡ ነኝ ፡ እያለ ፡ የሚያበረታኝን
እንደጌታዬ ፡ እንደኢየሱስ ፡ ከወዴት ፡ ላግኝ
በለመለመው ፡ መስክ ፡ ሚመራኝ ፡ በእረፍት ፡ ውኃ ዘንድ
አላገኝም ፡ በየትም ፡ ስፍራ ፡ እኔን ፡ የሚወድ