From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ምንድን ፡ ነው ፡ የመኖር ፡ ትርጉሙ ፡ የሕይወት ፡ ጣዕሙ
ምንድን ፡ ነው ፡ ሃብትን ፡ ማካበቱ ፡ ዓለምን ፡ ማትረፉ
ምንድን ፡ ነው ፡ ክብር ፡ ዝና ፡ ማግኘት ፡ ፊደልን ፡ መቁጠሩ
ምንድን ፡ ነው ፡ ውበት ፡ ወጣትነት ፡ ጉብዝናው ፡ ጥቅሙ
አዝ፦ አንተን ፡ ካላከበሩ (፬x)
አንተን ፡ ካላከበሩ (፬x)
ምንድን ፡ ነው ፡ የቃል ፡ ዕውቀት ፡ እድገት ፡ የአገልግሎት ፡ ብዛት
ምንድን ፡ ነው ፡ ቀን ፡ ከሌት ፡ መሮጡ ፡ ሰውን ፡ ለማስደሰት
ምንድን ፡ ነው ፡ በሥጋ ፡ ለባሽ ፡ መከበር ቅዱሱ ፡ መንፈስህ ፡ ሳይኖር
ምንድን ፡ ነው (፫x)
አዝ፦ አንተን ፡ ካላከበሩ (፬x)
አንተን ፡ ካላከበሩ (፬x)
ምንድን ፡ ነው ፡ ስለእኔ ፡ ሳይሆን
ምንድን ፡ ነው ፡ ሕይወቴ ፡ በሙሉ ፡ ካላከበረህ ፡ እንዲሁ
ምንድን ፡ ነው ፡ መድከሚ ፡ ምንድን ፡ ነው ፡ ጥቅሙ
ምንድን ፡ ነው ፡ አላማዬ ፡ ካልሆንከኝ ፡ ኢየሱስ
ከንቱ ፡ ነው (፬x)
ከንቱ ፡ ነው (፬x)
አዝ፦ አንተን ፡ ካላከበሩ (ከንቱ ፡ ነው) (፬x)
አንተን ፡ ካላከበሩ (ከንቱ ፡ ነው) (፬x)
|