አመልክሃለሁ (Amelkehalehu) - አውታሩ ፡ ከበደ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አውታሩ ፡ ከበደ
(Awtaru Kebede)

Awtaru Kebede 5.jpeg


(5)

ይቅርታ
(Yeqerta)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፪ (2010)
ቁጥር (Track):

፲ ፩ (11)

ርዝመት (Len.): 5:33
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአውታሩ ፡ ከበደ ፡ አልበሞች
(Albums by Awtaru Kebede)

ሞልቶ ፡ ለማይሞላ ፡ ለዚህ ፡ ዓለም ፡ ጉዳይ (፪x)
ጊዜ ፡ አላጠፋም ፡ ጐዶሎዬን ፡ ሳይ (፪x)
የበረከት ፡ ምንጩ ፡ መንገዱ ፡ ገብቶኛል (፪x)
ሁኔታው ፡ እያለ ፡ አምልከኝ ፡ ብሎኛል (፪x)

ልቤም ፡ እንዲህ ፡ ይለኛል
ኧረ ፡ ተነስ ፡ ይለኛል
አምልክ ፡ አምልክ ፡ ይለኛል
አመልክሃለሁ ፡ ጌታዬ ፡ አመልክሃለሁ
አመልክሃለሁ ፡ ኢየሱስ ፡ አመልክሃለሁ (፪x)

ተይ ፡ አልኳት ፡ ነፍሴን ፡ ተይ ፡ እንጂ (፪x)
ኢየሱስ ፡ ቆሞ ፡ ከደጅ
መዘመር ፡ ማምለክ ፡ ነው ፡ እንጂ (፪x)

አንተ ፡ የእግዚአብሔር ፡ ልጅ
ዛሬም ፡ መጣሁ ፡ ወደ ፡ ደጅህ
ምህረትህ ፡ በዝቶልኝ ፡ በሕይወቴ
ያቆመኝ ፡ ፀጋህ ፡ ነው ፡ መድኃኒቴ

አሁን ፡ አሁንማ ፡ እየዋለ ፡ ሲያድር (፪x)
ይገርመኝ ፡ ጀመረ ፡ የመስቀሉ ፡ ፍቅር (፪x)
ልቤን ፡ ያደረገው ፡ የዝማሬ ፡ ጓዳ (፪x)
ለካስ ፡ ተምሬ ፡ ነው ፡ የለብኝም ፡ ዕዳ (፪x)

ልቤም ፡ እንዲህ ፡ ይለኛል
ኧረ ፡ ተነስ ፡ ይለኛል
አምልክ ፡ አምልክ ፡ ይለኛል
አመልክሃለሁ ፡ ጌታዬ ፡ አመልክሃለሁ
አመልክሃለሁ ፡ ኢየሱስ ፡ አመልክሃለሁ (፪x)