የእኔማ (Yeniema) - አውታሩ ፡ ከበደ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አውታሩ ፡ ከበደ
(Awtaru Kebede)

Awtaru Kebede 6.jpg


(6)

ወደፊት
(Wedefit)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፰ (2015)
ቁጥር (Track):

(1)

ርዝመት (Len.): 6:40
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአውታሩ ፡ ከበደ ፡ አልበሞች
(Albums by Awtaru Kebede)

የእኔማ ፣ የእኔማ ፡ ሰላም ፡ የእኔማ
የእኔማ ፣ የእኔማ ፡ ደስታ ፡ የእኔማ (፪x)

ከዚህ ፡ ዓለም ፡ አይደለም ፡ በመንፈሱ ፡ ነው
በብርም ፡ በወርቅም ፡ የማይገዛው
በወንጌል ፡ ሞኝነት ፡ በአመንኩት ፡ ቃል
ሰላሙ ፡ ከሆዴ ፡ ይፍለቀለቃል

አገዘኝ ፡ አገዘኝ (፰x)

ጠላቴ ፡ ዓይኑ ፡ እያየ
በመንፈሱ ፡ ነካኝ ፡ አትረፈረፈኝ
አገር ፡ ምድሩ ፡ እያየ
በቅባቱ ፡ ነካኝ ፡ አትረፈረፈኝ

አገዘኝ ፡ አገዘኝ (፰x)

ላምልክህ ፡ ደግሜ ፡ እስኪ ፡ ደግሜ ፡ ደጋግሜ (አሄ)
ላምልክህ ፡ ደግሜ ፡ እስኪ ፡ ደግሜ ፡ ደጋግሜ (፪x)

ይውጣ ፡ ወደላይ ፡ ከድንኳኔ
የአምልኮ ፡ የዝማሬው ፡ ቅኔ
የሆንክልኝን ፡ ሳስበው
ከዚህ ፡ በላይ ፡ ምን ፡ አለ ፡ ምሆነው

ከፍ ፡ በልልኝ (፬x)
ደምቀህ ፡ ታይልኝ (፬x)

ና ፡ ሲለኝ ፡ ቃሉን ፡ ተማምኖ ፡ በውኃው ፡ ላይ
ና ፡ ሲለኝ ፡ እጁ፡ እንደማይጥል ፡ አታዩም ፡ ወይ
ና ፡ ሲለኝ ፡ ከሁኔታ ፡ ጋር ፡ እርሱ ፡ አይለካ
ና ፡ ሲለኝ ፡ መንገድ ፡ ይሆናል ፡ ውኃውም ፡ ለካ

ጠላቴ ፡ ዓይኑ ፡ እያየ
በመንፈሱ ፡ ነካኝ ፡ አትረፈረፈኝ
አገር ፡ ምድሩ ፡ እያየ
በእሳቱ ፡ ነካኝ ፡ አትረፈረፈኝ

አገዘኝ ፡ አገዘኝ (፰x)

የእኔማ ፡ የእኔማ ፡ ሰላም ፡ የእኔማ
የእኔማ ፡ የእኔማ ፡ ደስታ ፡ የእኔማ (፪x)

ከዚህ ፡ ዓለም ፡ አይደለም ፡ በመንፈሱ ፡ ነው
በብርም ፡ በወርቅም ፡ የማይገዛው
በወንጌል ፡ ሞኝነት ፡ በአመንኩት ፡ ቃል
ሰላሙ ፡ ከሆዴ ፡ ይፍለቀለቃል

አገዘኝ ፡ አገዘኝ (፰x)

ላምልክህ ፡ ደግሜ ፡ እስኪ ፡ ደግሜ ፡ ደጋግሜ (አሄ)
ላምልክህ ፡ ደግሜ ፡ እስኪ ፡ ደግሜ ፡ ደጋግሜ (፪x)

ይውጣ ፡ ወደላይ ፡ ከድንኳኔ
የአምልኮ ፡ የዝማሬው ፡ ቅኔ
የሆንክልኝን ፡ ሳስበው
ከዚህ ፡ በላይ ፡ ምን ፡ አለ ፡ ምሆነው

ከፍ ፡ በልልኝ (፬x)
ደምቀህ ፡ ታይልኝ (፬x)