ክበር ፡ አንተ ፡ ብቻ (Keber Ante Becha) - አስቴር ፡ ዮሴፍ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አስቴር ፡ ዮሴፍ
(Aster Yosef)

Aster Yosef 3.jpg


(3)

አንተው ፡ ትሻለኛለህ
(Antew Teshalegnaleh)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2006)
ቁጥር (Track):

(1)

ርዝመት (Len.): 4:54
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአስቴር ፡ ዮሴፍ ፡ አልበሞች
(Albums by Aster Yosef)

እነዚያስ ፡ ያንን ፡ የተማመኑበት
ተሰነካከለ ፡ ተስፋ ፡ ያደረጉበት
ክብራቸው ፡ ወደቀ ፡ ቀንዳቸው ፡ ተመታ
በዙፋኑ ፡ ከብሮ ፡ አለ ፡የእኛ ፡ ጌታ
ብቻህን ፡ ተዐምራት ፡ ያደረግህ ፡ ጌታ
ፍፁም ፡ የማትረታ

አዝ፦ በሠማይ ፡ በምድር ፡ ከቶ ፡ የለህ ፡ አቻ
ክበር ፡ አንተ ፡ ብቻ ፡ ንገሥ ፡ አንተ ፡ ብቻ

ሠማይን ፡ እንደ ፡ መጋረጃ ፡ ዘርግቶ
እልፍኙን ፡ በውኃ አሳምሮ ፡ ሰርቶ
ምንም ፡ የሌለበት ፡ እጅግ ፡ ከደረቀ
አለቱን ፡ ሰንጥቆ ፡ ውሃን ፡ አፈለቀ (፪x)

አዝ፦ በሠማይ ፡ በምድር ፡ ከቶ ፡ የለህ ፡ አቻ
ክበር ፡ አንተ ፡ ብቻ ፡ ንገሥ ፡ አንተ ፡ ብቻ

ሸለቆን ፡ የሚሞላ ፡ ተራራን ፡ የሚንድ
አገልጋዩን ፡ እንደ ፡ ነበልባል ፡ የሚያነድ
በተራሮች ፡ ላይ ፡ ውሆችን ፡ የሚያቆም
እንደ ፡ እግዚአብሔር ፡ ያለ ፡ ታላቅ ፡ አምላክ ፡ የለም

አዝ፦ በሠማይ ፡ በምድር ፡ ከቶ ፡ የለህ ፡ አቻ
ክበር ፡ አንተ ፡ ብቻ ፡ ንገሥ ፡ አንተ ፡ ብቻ

በሚንበለበለው ፡ እሳት ፡ ውስጥ ፡ ቢከተን
የምታምኑት ፡ አምላክ ፡ ያድናችሁ ፡ ቢለን
የምናምነው ፡ አምላክ ፡ ዝም ፡ ብሎ ፡ አያየን
ነጥቆ ፡ ያወጣናል ፡ ከእሳቱ ፡ ወላፈን (፪x)

አዝ፦ በሠማይ ፡ በምድር ፡ ከቶ ፡ የለህ ፡ አቻ
ክበር ፡ አንተ ፡ ብቻ ፡ ንገሥ ፡ አንተ ፡ ብቻ

መዝገቡም ፡ ይከፈት ፡ ታሪክም ፡ ይመርመር
አንደበትም ፡ ያውራ ፡ መስካሪም ፡ ይመስክር
ብርቱ ፡ የሆነ ፡ አምላክ ፡ ማነው ፡ ከአንተ ፡ በቀር
የሚነደውን ፡ እሳት ፡ በእሳት ፡ የሚሽር (፪x)

አዝ፦ በሠማይ ፡ በምድር ፡ ከቶ ፡ የለህ ፡ አቻ
ክበር ፡ አንተ ፡ ብቻ ፡ ንገሥ ፡ አንተ ፡ ብቻ