መንፈስ ፡ ቅዱስ (Menfes Qedus) - አስቴር ፡ አበበ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አስቴር ፡ አበበ
(Aster Abebe)

Aster Abebe 1.jpg


(1)

ክብር ፡ የበቃህ ፡ ነህ
(Keber Yebeqah Neh)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፱ (2017)
ቁጥር (Track):

(6)

ርዝመት (Len.): 4:43
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአስቴር ፡ አበበ ፡ አልበሞች
(Albums by Aster Abebe)

አለህ ፡ በውስጤ ፡ ሰላምህ ፡ በዝቶልኛል
አለህ ፡ በላዬ ፡ ድል ፡ ማድረግ ፡ ሆኖልኛል
አለህ ፡ ከጎኔ ፡ ስትረዳኝ ፡ አየሁህ
አለህ ፡ በቤቴ ፡ ህይወቴን ፡ አጣፈጥህ (፪x)

አዝ፦ መንፈስ ፡ ቅዱሰ ፡ መጽናኛዬ
አቅሜ ፡ ነህ ፡ ጉልበት ፡ ሃይሌ
አማላጄ ፡ ነህ ፡ ደጀኔ
አቅም ሀይሌ ፡ ጓደኛዬ

አንድ ፡ የሆነ ፡ ጉዳይ ፡ ከእኔ ፡ ጋር ፡ እስክትጨርስ ፡ ድረስ
አይደለም ፡ ለጊዜ ፡ ወደ ፡ አብ ፡ እስከምትመለስ
ሁሌም ፡ ክእኔ ፡ ጋር ፡ ነህ ፡ ሆነሃል ፡ ወዳጄ
በውስጤ ፡ በላዬ ፡ ከጎኔ ፡ ከደጄ (፪x)

አዝ፦ መንፈስ ፡ ቅዱሰ ፡ መጽናኛዬ
አቅሜ ፡ ነህ ፡ ጉልበት ፡ ሃይሌ
አማላጄ ፡ ነህ ፡ ደጀኔ
መበርቻዬ ፡ ጓደኛዬ

እውርነት ፡ ቀርቶ ፡ ማየት ፡ ጀምሬያለሁ
የልቦናዬን ፡ አይኖች ፡ በአንተን ፡ አግኝቻለሁ
ድፍርሱን ፡ ህይወቴን ፡ በምክርህ ፡ አጥርተሃል
ያላንተ ፡ እንደማልኖር ፡ ልቤ ፡ ይህን ፡ አውቋል (፪x)

አዝ፦ መንፈስ ፡ ቅዱሰ ፡ መበርቻዬ
አቅሜ ፡ ነህ ፡ ጉልበት ፡ ሃይሌ
አማላጄ ፡ ነህ ፡ ደጀኔ
አቅሜ ፡ ኃይሌ ፡ ጓደኛዬ
መጽናኛዬ ፡ ጓደኛዬ
አለኝታዬ ፡ ጓደኛዬ
መበርቻዬ ፡ መጽናኛዬ
አለኝታዬ ፡ ጕደኛዬ