አስይዘኝ ፡ መስቀሉን (Asyizegn Meskelun) - አሉላ ፡ ጌታሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
Broom.png ይህ ፡ ጽሑፍ ፡ ገና ፡ አልተረጋገጠም ። እርማቶች ፡ ሊያስፈልጉት ፡ ይችላል ። ከቻሉ ፡ እርስዎ ፡ ያሻሽሉት
አሉላ ፡ ጌታሁን
(Alula Getahun)

Alula Getahun 1.jpg


(1)

አስይዘኝ ፡ መስቀሉን
(Asyizegn Meskelun)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፲ (2018)
ቁጥር (Track):

(7)

ርዝመት (Len.): 5:38
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአሉላ ፡ ጌታሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Alula Getahun)

ያልተቀበልነው - ምን ምን አለ?
ሁሉ በርሱ ነው - ሞላ፥ ጎደለ
ለገባው ቃሉ - የታመነ
እግዚአብሔር ነው - የገነነ

እግዚአብሔር ብቻ ነው - የመስጠት ልኩ
ተቀብላችሁ - ክብሩን አትንኩ
ቢጎል ቢሞላ - ለነፍስ ዋስትና
ሲጠማን ምንጭ ነው - ሲርበን መና! - [አዝ]

ደከመኝ አይል - አጋዥ አይሻ
በራሱ ሙሉ - የራሱ ጋሻ
ታክቶት አላየን - እንደዛለ ሰው
አንዴም አልሰማን - ጉልበቱ ሲያንሰው!

[አዝ]

ይኼ ማን ነው - ባህር ያቆመ
የህዝቡን ማዳን - የፈፀመ?
ኧረ ይህ ማን ነው - የማዕዘን አለት
ፍጥረታት ሁሉ - የሚገዙለት?

በ'ፍኙ የሚሰፍር - ያሉትን ቀላያት
በምድርም ያሉ - የሰማይም ሰማያት፤
በኃይል የታሰሩትን - ፈቶ የለቀቀ
የሚጋፉን ዓለማት - ሰብስቦ ያረቀ!

ጫንቃችን ላይ በዝቶ - የኃጢያት እዳችን
በፍርድ ስር ሳለን - መውጫ መንገዳችን፤
የብርሃን መገኛ - የሰው ልብ ያበራ
የፍጥረት ፈጣሪ - ማዳኑን የሰራ!

እግዚአብሔር ብቻ ነው - የመስጠት ልኩ
ተቀብላችሁ - ክብሩን አትንኩ
ቢጎል ቢሞላ - ለነፍስ ዋስትና
ሲጠማን ምንጭ ነው - ሲርበን መና!

በ'ፍኙ የሚሰፍር - ያሉትን ቀላያት
በምድርም ያሉ - የሰማይም ሰማያት፤
የብርሃን መገኛ - የሰው ልብ ያበራ
የፍጥረት ፈጣሪ - ማዳኑን የሰራ!

ኢየሱስ ክርስቶስ - መድኅኒተ አለሙ
በፍጥረት ሁሉ ፊት - ገናና ነው ስሙ። 2x