አልወርድም (Alwerdem) - አዲስዓለም ፡ አሰፋ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዲስዓለም ፡ አሰፋ
(Addisalem Assefa)

Addisalem Assefa 3.jpg


(3)

ያመለጠ ፡ እኔ ፡ ነኝ
(Yamelete Enie Negn)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፭ (2013)
ቁጥር (Track):

(9)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዲስዓለም ፡ አሰፋ ፡ አልበሞች
(Albums by Addisalem Assefa)

አስገረመኝ/አስደነቀኝ ፡ ነገሬን ፡ ውብ ፡ አረገና
አፌን ፡ ሞላው ፡ በአዲስ ፡ ቅኔ ፡ በምሥጋና
በዝማሬ ፡ እገባለሁ ፡ ወደ ፡ ቤቱ
ሥራዬ ፡ ተሰርቷልና ፡ በምረቱ

ኃይሌን ፡ አድሶት ፡ ጌታዬ ፡ ወጥቻለሁ ፡ አሃሃ ፡ ነቅቻለሁ
ከዚያ ፡ ላይ ፡ ማን ፡ ያወርደኛል ፡ ከፍ ፡ ብያለሁ ፡ አሃሃ ፡ ከፍ ፡ ብያለሁ
ጠላቴ ፡ አታገኘኝም ፡ በትላንቱ ፡ በትላንቱ
ኢየሱስ ፡ መጥቶ ፡ አውጥቶኛል ፡ በሰዓቱ ፡ በሰዓቱ
በሰዓቱ ፡ በሰዓቱ (፬x)

የማታ ፡ ለቅሶዬ ፡ ጠዋት ፡ ተለውጦ
እንደ ፡ መርደኪዮስ ፡ ታሪክ ፡ ነገር ፡ ተገልብጦ
በኮረብታ ፡ ሆኜ ፡ መዝሙር ፡ ዘምራለሁ ፡ ሆ
እኔ ፡ ከላይ ፡ ሆኜ ፡ ጠላቴን ፡ ረግጫለሁ

አልወርድም ፡ ከከፍታዬ ፡ ላይ
እግዚአብሔር ፡ አርጐኛል ፡ የበላይ
ዝቅታው ፡ ያንተ ፡ ነው ፡ ጠላቴ
እግዚአብሔር ፡ ጥሎሃል ፡ ከፊቴ

እግዚአብሔር ፡ ቀኑን ፡ እስኪሰጥ ፡ ድረስ
አይኔ ፡ ዝም ፡ ብሎ ፡ እምባን ፡ ቢያፈስ
እንዳለቀስኩኝ ፡ መቼ ፡ ቀረሁኝ
የምስቅበት ፡ ዘመን ፡ መጣልኝ
አፌን ፡ ምሥጋና ፡ ኦሆ ፡ ይኸው ፡ ሞላኝ (፪x)

አልወርድም ፡ ከከፍታዬ ፡ ላይ
እግዚአብሔር ፡ አርጐኛል ፡ የበላይ
ዝቅታው ፡ ያንተ ፡ ነው ፡ ጠላቴ
እግዚአብሔር ፡ ጥሎሃል ፡ ከፊቴ

የእግዚአብሔር ፡ ጉልበት ፡ የክንዱ ፡ ብርታት
ይህንን ፡ አድርጓል ፡ ሰርቶ ፡ ታምራት
ክፉ ፡ በሆኑት ፡ ቀናቶች ፡ ፈንታ
ደስታ ፡ አጠገበኝ ፡ ኤልሻዳዩ ፡ ጌታ
አመልከዋለሁ ፡ ሁሌ ፡ ጠዋት ፡ ማታ (፪x)

ኃይሌን ፡ አድሶት ፡ ጌታዬ ፡ ወጥቻለሁ ፡ አሃሃ ፡ ነቅቻለሁ
ከዚያ ፡ ላይ ፡ ማን ፡ ያወርደኛል ፡ ከፍ ፡ ብያለሁ ፡ አሃሃ ፡ ከፍ ፡ ብያለሁ
ጠላቴ ፡ አታገኘኝም ፡ በትላንቱ ፡ ኦሆሆ ፡ በትላንቱ
ኢየሱስ ፡ መጥቶ ፡ አውጥቶኛል ፡ በሰዓቱ ፡ ኦሆሆ ፡ በሰዓቱ
በሰዓቱ ፡ በሰዓቱ (፬x)

ልቤን ፡ አልጥልም ፡ ከጠፉት ፡ አህዮች ፡ ላይ
እግዚአብሔር ፡ መጥቷል ፡ ሊሰጠኝ ፡ ከዚያ ፡ በላይ
ሃሳቡ ፡ ለእኔ ፡ ምንጊዜም ፡ የመልካም ፡ ነው
ታምር ፡ ሲሰራ ፡ በሕይወቴ ፡ አይቻለሁ

አልወርድም ፡ ከከፍታዬ ፡ ላይ
እግዚአብሔር ፡ አርጐኛል ፡ የበላይ
ዝቅታው ፡ ያንተ ፡ ነው ፡ ጠላቴ
እግዚአብሔር ፡ ጥሎሃል ፡ ከፊቴ