የጠበኩት ፡ ጌታ (Yetebekut Gieta) - አዲስዓለም ፡ አሰፋ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዲስዓለም ፡ አሰፋ
(Addisalem Assefa)

Addisalem Assefa 2.jpg


(2)

ሰባሪው ፡ ጌታ ፡ ከፊቴ ፡ ወጥቷል
(Sebariw Gieta Kefitie Wettual)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፩ (2008)
ቁጥር (Track):

(4)

ርዝመት (Len.): 5:20
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዲስዓለም ፡ አሰፋ ፡ አልበሞች
(Albums by Addisalem Assefa)

የጠበኩት ፡ ጌታ ፡ ድንገት ፡ ይመጣል (፪x)
አሜን ፡ ድንገት ፡ ይመጣል ፡ ሁሉን ፡ ዉብ ፡ ያደርጋል
የጠበኩት ፡ ጌታ ፡ ድንገት ፡ ይመጣል (፪x)
እሰይ ፡ ድንገት ፡ ይመጣል ፡ ሁሉን ፡ ዉብ ፡ ያደርጋል

ዞር ፡ በል ፡ ጠላቴ ፡ አትነዝንዘኝ ፡ ዞር ፡ በልልኝ
መቼ ፡ ሊረሳኝ ፡ ነው ፡ እግዚአብሔር ፡ አባት ፡ የሆነኝ
ስንቱን ፡ አልፌያለሁ ፡ በእርሱ ፡ ብርታት ፡ በጀርባው ፡ አዝሎኝ
አሁንም ፡ ታማኝ ፡ ነው ፡ የእኔ ፡ ጌታ ፡ ፈጥኖ ፡ ሊረዳኝ

አልተውሽም ፡ ብሎ ፡ ተናግሮኛል
እንደሱ ፡ እውነተኛ ፡ የት ፡ ይገኛል (፪x)
ያስጨበጠንኝ ፡ ቃል ፡ እየዛለሁ
በቃሉ ፡ ይገኛል ፡ አምነዋለሁ
በቃሉ ፡ ይገኛል ፡ አምነዋለሁ (፪x)

ድንገት ፡ ይመጣል ፡ (ድንገት ፡ ይመጣል)
ድንገት ፡ ይመጣል ፡ አሜን
ድንገት ፡ ይመጣል ፡ ሁሉን ፡ ይለውጣል (፫x)

ድንገት ፡ ሲመጣ ፡ አሃ ፡ አሃሃ ፡ ወደ ፡ መቅደሱ
እምባን ፡ በማበስ ፡ አሃ ፡ አሃሃ ፡ ማነው ፡ እንደሱ
ሰብሬ ፡ አልፋለሁ ፡ አሃ ፡ አሃሃ ፡ የነሃሱን ፡ ደጃፍ
መቆም ፡ አልሻም ፡ ከቶ ፡ ጌታ ፡ ስለሚያልፍ

ድንገት ፡ ይመጣል ፡ (ድንገት ፡ ይመጣል)
ድንገት ፡ ይመጣል ፡ አሜን
ድንገት ፡ ይመጣል ፡ ሁሉን ፡ ይለውጣል

ድንገት ፡ ይመጣል ፡ (ድንገት ፡ ይመጣል)
ድንገት ፡ ይመጣል ፡ እሰይ
ድንገት ፡ ይመጣል ፡ ሁሉን ፡ ይለውጣል

እርሱን ፡ ብዬ ፡ የምን ፡ ጭንቀት ፡ እሱን ፡ ብዬ ፡ (እሱን ፡ ብዬ)
ያለስጋት ፡ ልቀመጥ ፡ እንጂ ፡ ተዘልዬ (፪x)

ቢዘገይም ፡ እኮ ፡ በርግጥ ፡ ይመጣል ፡ (ይመጣል)
ሁሉን ፡ ነገሬን ፡ አዲስ ፡ ያደርጋል ፡ (አዲስ ፡ ያደርጋል)
በቀጠረው ፡ ሰዓት ፡ በራሱ ፡ ጊዜ ፡ (በራሱ ፡ ጊዜ)
በእርሱ ፡ ይገሠጻል ፡ ሃዘን ፡ ትካዜ (፪x)

እሱን ፡ ብዬ ፡ የምን ፡ ጭንቀት ፡ እሱን ፡ ብዬ ፡ (እሱን ፡ ብዬ)
ያለስጋት ፡ ልቀመጥ ፡ እንጂ ፡ ተዘልዬ (፪x)

ቢዘገይም ፡ እኮ ፡ በርግጥ ፡ ይመጣል ፡ (ይመጣል)
ሁሉን ፡ ነገሬን ፡ አዲስ ፡ ያደርጋል ፡ (አዲስ ፡ ያደርጋል)
በቀጠረው ፡ ሰዓት ፡ በራሱ ፡ ጊዜ (በራሱ ፡ ጊዜ)
በእርሱ ፡ ይገሠጻል ፡ ሃዘን ፡ ትካዜ (፪x)