ይገባሃል (Yegebahal) - አዲስዓለም ፡ አሰፋ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዲስዓለም ፡ አሰፋ
(Addisalem Assefa)

Addisalem Assefa 2.jpg


(2)

ሰባሪው ፡ ጌታ ፡ ከፊቴ ፡ ወጥቷል
(Sebariw Gieta Kefitie Wettual)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፩ (2008)
ቁጥር (Track):

(5)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዲስዓለም ፡ አሰፋ ፡ አልበሞች
(Albums by Addisalem Assefa)

አከብርሃለሁ ፡ በምሥጋና (፫x)
(ንጉሤ ፡ ነህና) ፡ ጌታዬ ፡ ነህና
አነግስሃለሁ ፡ በምሥጋና (፫x)
(ንጉሤ ፡ ነህና) ፡ ንጉሤ ፡ ነህና
 
አዝ፦ ይገባሃል ፡ ይገባሃል ፡ ይገባሃል
አሸንፈሃል ፡ አሸንፈሃል (፪x)

ዝቅ ፡ ብዬ ፡ ላክብርህ ፡ አሃሃሃ ፡ ላክብርህ
በልቤ ፡ ላይ ፡ ልሹምህ ፡ ኦሆሆሆ ፡ ልሹምህ
(ከአንተ፡ በላይ) ከአንተ ፡ ሌላ ፡ የለምና ፡ አሃሃሃ ፡ የለምና
እንካ ፡ ክበር ፡ በምሥጋና ፡ ኦሆሆሆ ፡ በምሥጋና

አከብርሃለሁ ፡ በምሥጋና (፫x)
(ንጉሤ ፡ ነህና) ፡ ጌታዬ ፡ ነህና
አነግስሃለሁ ፡ በምሥጋና (፫x)
(ንጉሤ ፡ ነህና) ፡ ንጉሤ ፡ ነህና

አዝ፦ ይገባሃል ፡ ይገባሃል ፡ ይገባሃል
አሸንፈሃል ፡ አሸንፈሃል (፪x)

እግሬን ፡ በሰላም ፡ መንገድ ፡ አቅንተህልኛል
ያጐበጠኝን ፡ ቀንበር ፡ ሰባብረህልኛል
በአንተ ፡ ላይ ፡ ተስፋ ፡ አፍርቼ ፡ ጣፋጭ ፡ ፍሬ ፡ አፍርቻለሁ
ምሕረትህ ፡ ደግፎኝ ፡ ይሄው ፡ በሕይወት ፡ ኖሬያለሁ

አከብርሃለሁ ፡ በምሥጋና (፫x)
(ንጉሤ ፡ ነህና) ፡ ጌታዬ ፡ ነህና
አነግስሃለሁ ፡ በምሥጋና (፫x)
(ንጉሤ ፡ ነህና) ፡ ንጉሤ ፡ ነህና

አዝ፦ ይገባሃል ፡ ይገባሃል ፡ ይገባሃል
አሸንፈሃል ፡ አሸንፈሃል (፪x)