እንዴት ፡ እፈራለሁ (Endiet Eferalehu) - አዲስዓለም ፡ አሰፋ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዲስዓለም ፡ አሰፋ
(Addisalem Assefa)

Addisalem Assefa 2.jpg


(2)

ሰባሪው ፡ ጌታ ፡ ከፊቴ ፡ ወጥቷል
(Sebariw Gieta Kefitie Wettual)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፩ (2008)
ቁጥር (Track):

(8)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዲስዓለም ፡ አሰፋ ፡ አልበሞች
(Albums by Addisalem Assefa)

ተጨንቃ ፡ ለነበረች ፡ ነፍሴ ፡ ጨለማን ፡ አይሆንም ፡ ሲል
አዋጅን ፡ በአዋጅ ፡ ሽሮ ፡ መርዶዬን ፡ ሲከለክል
ከፊቴ ፡ ቀድሞ ፡ ሲወጣ ፡ ተራራን ፡ ሲደለድል
ሥራዬን ፡ ሰርቶ ፡ ሲጨርስ ፡ ችግሬን ፡ ሲጠቀልል

መቃብሬን ፡ ሲከፍተው ፡ ታምር ፡ ሲሰራ
ነፍሴን ፡ እጅግ ፡ ሲያስጨንቅ ፡ በእኔ ፡ ሲፈራ
ታምራት ፡ ሲያስለምደኝ ፡ ሲያሳየኝ ፡ ኖሬ
እንዴት ፡ እሸበራለሁ ፡ እፈራለሁ ፡ ዛሬ

አዝ፦ እንዴት ፡ እንዴት ፡ እፈራለሁ (፫x)
ለምን ፡ ለምን ፡ እሰጋለሁ (፫x)
የተሸከመኝ ፡ ትልቅ ፡ አምላክ ፡ ነው (፬x)

ስንቱን ፡ ሸለቆ ፡ ስንቱን ፡ ተራራ
ጥሼ ፡ ሄጃለሁ ፡ ከእርሱ ፡ ጋራ (፪x)
እያሪኮዬ ፡ ቅጥሩ ፡ ሲፈርስ
አይታለች ፡ ነፍሴ ፡ በኢየሱስ (፪x)

ስለዚህ ፡ አልፈራም ፡ ምድር ፡ ብትናወጥ
በዙፋኑ ፡ እያለ ፡ ከቶ ፡ ከቶ ፡ ማይናወጥ (፪x)

በዙፋኑ ፡ እያለ ፡ ከቶ ፡ ከቶ ፡ ማይናወጥ (፪x)

አዝ፦ እንዴት ፡ እንዴት ፡ እፈራለሁ (፫x)
ለምን ፡ ለምን ፡ እሰጋለሁ (፫x)
የተሸከመኝ ፡ ትልቅ ፡ አምላክ ፡ ነው (፬x)

በእሳት ፡ ማሃል ፡ መንገድ ፡ ያለው ፡ ጌታ
መቼ ፡ ትቶኝ ፡ ያውቃል ፡ አንድ ፡ አፍታ
ማዕበልና ፡ ወጀቡን ፡ አራምዶ
ያሻግረኛል ፡ ከባህር ፡ ማዶ

ስለዚህ ፡ አልፈራም ፡ ምድር ፡ ብትናወጥ
በዙፋኑ ፡ እያለ ፡ ከቶ ፡ ከቶ ፡ ማይናወጥ (፪x)

በዙፋኑ ፡ እያለ ፡ ከቶ ፡ ከቶ ፡ የማይናወጥ (፪x)

አዝ፦ እንዴት ፡ እንዴት ፡ እፈራለሁ (፫x)
ለምን ፡ ለምን ፡ እሰጋለሁ (፫x)
የተሸከመኝ ፡ ትልቅ ፡ አምላክ ፡ ነው (፬x)