በኪሩቤል ፡ ላይ (Bekirubel Lay) - አብርሃም ፡ እና ፡ እያሱ ፡ ተክለማሪያም

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አብርሃም ፡ እና ፡ እያሱ ፡ ተክለማሪያም
(Abraham and Eyasu Teklemariam)

Abraham and Eyasu Teklemariam 2.jpg


(2)

ዘመናት ፡ አይለውጡህም
(Zemenat Aylewetuhem)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፪ (2010)
ቁጥር (Track):

(9)

ርዝመት (Len.): 4:21
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአብርሃም ፡ እና ፡ እያሱ ፡ ተክለማሪያም ፡ አልበሞች
(Albums by Abraham and Eyasu Teklemariam)

ከሰማያት ፡ በላይ ፡ በክብር ፡ ላለኸው
ለሞትና ፡ ለሲዖል ፡ ኃይልህን ፡ ያስታወቅከው
የዘላለም ፡ ደጆች ፡ ላንተ ፡ ይከፈቱ
የጽድቅ ፡ ንጉሥ ፡ ግባ ፡ ዛሬም ፡ እንደ ፡ ጥንቱ

አዝ:- በኪሩቤል ፡ ላይ ፡ የምትቀመጥ
የነገሥታት ፡ ንጉሥ ፡ ኢየሱስ ፡ አንተ ፡ ታይ
በኪሩቤል ፡ ላይ ፡ የምትቀመጥ
የሰላም ፡ አለቃ ፡ ኢየሱስ ፡ አንተ ፡ ና
 
እንደተስፋ ፡ ቃልህ ፡ መጣህ ፡ ወደ ፡ ምድር
ለገባው ፡ ሚስጥሩ ፡ ታየ ፡ የአንተ ፡ ክብር
የማይሻር ፡ የጸና ፡ የትንቢት ፡ ቃል ፡ ይዘን
እስክትመጣ ፡ ኢየሱስ ፡ እንጠብቅሃለን
 
አዝ:- በኪሩቤል ፡ ላይ ፡ የምትቀመጥ
የነገሥታት ፡ ንጉሥ ፡ ኢየሱስ ፡ አንተ ፡ ታይ
በኪሩቤል ፡ ላይ ፡ የምትቀመጥ
የሰላም ፡ አለቃ ፡ ኢየሱስ ፡ አንተ ፡ ና
 
ሃሌሉያ ፡ (ሃሌሉያ) ፡ ሃሌሉያ ፡ (ሃሌሉያ)
በምሥጋና ፡ (በምሥጋና) ፡ እናንግሠው ፡ (እናንግሠው)
 
አዝ:- በኪሩቤል ፡ ላይ ፡ (በኪሩቤል ፡ ላይ) ፡ የምትቀመጥ
የነገሥታት ፡ ንጉሥ ፡ ኢየሱስ ፡ አንተ ፡ ታይ
በኪሩቤል ፡ ላይ ፡ (በኪሩቤል ፡ ላይ) ፡ የምትቀመጥ
የሰላም ፡ አለቃ ፡ ኢየሱስ ፡ አንተ ፡ ና (፬x)